https://amh.sputniknews.africa/20260623/4405763.html
የእስራኤል ወታደሮች በሶማሊላንድ መሠማራታቸው ተዘገበ
የእስራኤል ወታደሮች በሶማሊላንድ መሠማራታቸው ተዘገበ
Sputnik አፍሪካ
የእስራኤል ወታደሮች በሶማሊላንድ መሠማራታቸው ተዘገበእስራኤል በታህሳስ ወር ለሶማሊላንድ ነፃነት እውቅና በመስጠት የመጀመሪያዋ ሀገር ከሆነች ጥቂት ጊዜ በኋላ 50 ወታደሮችን ያቀፈ ኃይል ማሠማራቷን ሚዲያዎች አንድ ከፍተኛ የሶማሊያ ባለሥልጣንን ጠቅሰው... 23.06.2026, Sputnik አፍሪካ
2026-06-23T09:03+0300
2026-06-23T09:03+0300
2026-06-23T09:04+0300
sputnik africa
telegram sputnik_ethiopia
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07ea/06/17/4405610_0:109:1200:784_1920x0_80_0_0_039af0f2f8099d51ed0c797696675c23.jpg
የእስራኤል ወታደሮች በሶማሊላንድ መሠማራታቸው ተዘገበእስራኤል በታህሳስ ወር ለሶማሊላንድ ነፃነት እውቅና በመስጠት የመጀመሪያዋ ሀገር ከሆነች ጥቂት ጊዜ በኋላ 50 ወታደሮችን ያቀፈ ኃይል ማሠማራቷን ሚዲያዎች አንድ ከፍተኛ የሶማሊያ ባለሥልጣንን ጠቅሰው ዘግበዋል። የሶማሊያ ፕሬዚዳንት የደህንነት መረጃ አቅራቢ አብዱራህማን ሼክ አዝሃሪ፤ "የእስራኤል ወታደራዊ እና የደህንነት አባላት በሶማሊላንድ መገኘት አዲስ ነገር አይደለም። ከ2025 መጀመሪያ ጀምሮ በርበራ በሚገኘው የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ወታደራዊ ተቋም ውስጥ ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸው ነው የሚነገረው" ብለዋል። ተገንጥይዋ የሶማሊያ ክልል ወደ ኢራን ለሚደረጉ የረጅም ርቀት በረራዎች የሚያገለግል ወታደራዊ ጣቢያ ለእስራኤል ሳታመቻች እንዳልቀረ ተዘግቧል። እስራኤል በቀይ ባሕር የባሕር ኃይል ጦር ሠፈር ለመመስረት እንደምትፈልግም ይታመናል። "የሶማሊያ መንግሥት አሁን ስለሚቀጥለው እርምጃው በጥንቃቄ ማሰብ አለበት። [...] ይህ እስራኤል ከወደፊት የደህንነት ጥቅሞቿ ጋር በቀጥታ አገናኝታ የምታየው ሰፊ እና የረጅም ጊዜ ስትራቴጂካዊ ፕሮጀክት አካል ነው" ሲሉ አዝሃሪ በኤክስ ገጻቸው ጽፈዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
2026
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07ea/06/17/4405610_6:0:1195:892_1920x0_80_0_0_a4e6126c731c70fc148c0adb210942c2.jpgSputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
sputnik africa, telegram sputnik_ethiopia
sputnik africa, telegram sputnik_ethiopia
የእስራኤል ወታደሮች በሶማሊላንድ መሠማራታቸው ተዘገበ
09:03 23.06.2026 (የተሻሻለ: 09:04 23.06.2026) የእስራኤል ወታደሮች በሶማሊላንድ መሠማራታቸው ተዘገበ
እስራኤል በታህሳስ ወር ለሶማሊላንድ ነፃነት እውቅና በመስጠት የመጀመሪያዋ ሀገር ከሆነች ጥቂት ጊዜ በኋላ 50 ወታደሮችን ያቀፈ ኃይል ማሠማራቷን ሚዲያዎች አንድ ከፍተኛ የሶማሊያ ባለሥልጣንን ጠቅሰው ዘግበዋል።
የሶማሊያ ፕሬዚዳንት የደህንነት መረጃ አቅራቢ አብዱራህማን ሼክ አዝሃሪ፤ "የእስራኤል ወታደራዊ እና የደህንነት አባላት በሶማሊላንድ መገኘት አዲስ ነገር አይደለም። ከ2025 መጀመሪያ ጀምሮ በርበራ በሚገኘው የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ወታደራዊ ተቋም ውስጥ ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸው ነው የሚነገረው" ብለዋል።
ተገንጥይዋ የሶማሊያ ክልል ወደ ኢራን ለሚደረጉ የረጅም ርቀት በረራዎች የሚያገለግል ወታደራዊ ጣቢያ ለእስራኤል ሳታመቻች እንዳልቀረ ተዘግቧል። እስራኤል በቀይ ባሕር የባሕር ኃይል ጦር ሠፈር ለመመስረት እንደምትፈልግም ይታመናል።
"የሶማሊያ መንግሥት አሁን ስለሚቀጥለው እርምጃው በጥንቃቄ ማሰብ አለበት። [...] ይህ እስራኤል ከወደፊት የደህንነት ጥቅሞቿ ጋር በቀጥታ አገናኝታ የምታየው ሰፊ እና የረጅም ጊዜ ስትራቴጂካዊ ፕሮጀክት አካል ነው" ሲሉ አዝሃሪ በኤክስ ገጻቸው ጽፈዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X