“ጥሬ ቡናን ወደ ውጭ መላክ እያቆምን ነው” - የኬንያ ፕሬዚዳንት

ሰብስክራይብ

“ጥሬ ቡናን ወደ ውጭ መላክ እያቆምን ነው” - የኬንያ ፕሬዚዳንት

​ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን የሚያጠናክሩ፣ የገበያ ተደራሽነትን የሚያሻሽሉ እና የገበሬዎችን ገቢ የሚያስጠብቁ ማሻሻያዎች ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ የአንድ ኪሎ ቡና ዋጋን ከ0.23–0.54 ዶላር ወደ 0.92–1.23 ዶላር ከፍ ማድረጋቸውን ዊሊያም ሩቶ ገልጸዋል።

በኪሪንያጋ የሀገሪቱን የቡና ዘርፍ ለማነቃቃት በተዘጋጀ መርኃ-ግብር ማብሰሪያ ባደረጉት ንግግር፤ “ከእያንዳንዱ የቡና ሽያጭ ቢያንስ 80 በመቶው በቀጥታ ለገበሬው እንዲደርስ እያደረግን ሲሆን ክፍያም ሽያጭ በተፈጸመ በአምስት ቀናት ውስጥ ይፈጸማል” ብለዋል።

​ በተጨማሪም “ከፍተኛ እሴት በኬንያ እንዲቀር፤ ሀገሪቱ ትኩረቷን ወደ ሀገር ውስጥ ማቀነባበር፣ ማሸግ እና ብራንዲንግ ላይ እያደረገች ነው” ሲሉ ፕሬዚዳንቱ አስታውቀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0