- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ከሥራ ፈላጊነት ወደ ሀብት ፈጣሪነት፦ የአፍሪካ ትምህርት ሥርዓትና የዕውቀት ነጻነት

ከሥራ ፈላጊነት ወደ ሀብት ፈጣሪነት፦ የአፍሪካ ትምህርት ሥርዓትና የዕውቀት ነጻነት
ሰብስክራይብ
"የትምህርት ሥርዓታችን አሁንም ድረስ የራሳቸውን ሀብት የሚፈጥሩ ሉዓላዊ ዜጎችን ከመቅረጽ ይልቅ በሌሎች ላይ ጥገኞች የሆኑ የሥራ ፈላጊዎችን ስብስብ እያመረተ ይገኛል።... እውነተኛ ነጻነት የሚጀምረው የአፍሪካን የአገሬው ተወላጅ ዕውቀቶች እና ቋንቋዎች ለኢኮኖሚና ለዕውቀት ነጻነት ማዋል ስንችል ነው፡፡" ሲሉ የሌሴጎ ፋውንዴሽን መሥራች ሲቡሲሶ ማሻባኔ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን በክፍል አንድ የአፍሪካ የትምህርት ሥርዓት ከቅኝ ግዛት አስተሳሰብ ተላቆ አዳዲስ የሥራ ፈጣሪዎችን ለማፍራት መከተል ስላለበት የዕውቀት ምንጭ ከደቡብ አፍሪካው የለሴጎ ፋውንዴሽን መሥራች ከሲቡሲሶ ማሻባኔ ጋር ያደረግነውን ጥልቅ ውይይት ይዘን ቀርበናል። ክፍል ሁለት ደሞ አዲሱ ብሔራዊ የቱሪዝም ፖሊሲና ዓለም አቀፍ ገበያዎችን ለመሳብ ስላለው ዕቅድ፣ እንዲሁም እ.ኤ.አ ከሰኔ 20 እስከ ሰኔ 24 ፣ 2026 በኢትዮጵያ የቱሪስት አስጎብኝዎች “ኢትዮጵያ በቱሪስት አስጎብኝዎች ዓይን” በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ሙዚየም ለዕይታ የቀረበውን 4ኛው የፎቶግራፍ ዐውደ ርዕይን እንዳስሳለን። ዐዉደ ርዕዩ ቱሪዝምን ለማነቃቃት ስላለው ሚና የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ስለሺ ግርማ እና የኢትዮጵያ አስጎብኚዎች ማኅበር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሄኖክ ጸጋዬ ማብራሪያ ይሰጡናል።

ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0