ደቡብ አፍሪካ ከቻይና ጋር ያላትን የኢኮኖሚ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ትሻለች - ምክትል ፕሬዚዳንት ፖል ማሻቲሌ

ሰብስክራይብ

ደቡብ አፍሪካ ከቻይና ጋር ያላትን የኢኮኖሚ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ትሻለች - ምክትል ፕሬዚዳንት ፖል ማሻቲሌ

​ምክትል ፕሬዚዳንቱ በቻይና ዓለም አቀፍ የአቅርቦት ሰንሰለት ኤክስፖ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ "ይህ ዕቅድ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና የረጅም ጊዜ የኢንዱስትሪ ትብብርን ለማሳደግ ያለመ ነው" ብለዋል።

​ፖል ማሻቲሌ ቅድሚያ የሚሰጣቸው የትብብር መስኮችንም ዘርዝረዋል፦

​▪ ግብርና እና የምግብ ሥርዓቶች፣

​▪ ወሳኝ ማዕድናት እና አረንጓዴ ኢኮኖሚ፣

​▪ የላቀ ማኑፋክቸሪንግ፣ ሎጅስቲክ እና የአውቶሞቲቭ ዕሴት ሰንሰለቶች።

በሀገራቱ መካከል ያለው ግንኙነት፤ "እንደ ብሪክስ፣ የቻይና-አፍሪካ ትብብር ፎረም እና በሌሎች ባለብዙ ወገን መድረኮች" አማካኝነት መሻሻሉን ቀጥሏል።

​ ለጋራ ብልጽግና የተፈረመው የኢኮኖሚ አጋርነት ማዕቀፍ ስምምነት፤ ከቀረጥ ነፃ ዕድል ጋር ተዳምሮ የደቡብ አፍሪካ ምርቶች ወደ ቻይና ገበያ ያለምንም ቀረጥ እንዲገቡ እንደሚያስችልም አክለው ገልጸዋል።

​"ሀገራችንን ተመራጭ የኢንቨስትመንት መዳረሻ እና በዓለም አቀፍ የአቅርቦት ሰንሰለት አስተማማኝ የዕሴት ምንጭ ለማድረግ ቁርጠኛ ነን።"



በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0