ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በኢቦላ ወረርሽኝ ወቅት የሚሰጡ ‘ሁሉንም የጤና አገልግሎቶች' ነፃ አደረገች
19:59 21.06.2026 (የተሻሻለ: 20:04 21.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በኢቦላ ወረርሽኝ ወቅት የሚሰጡ ‘ሁሉንም የጤና አገልግሎቶች' ነፃ አደረገች
ይህ ውሳኔ የተላለፈው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተጠቂዎች በተመዘገቡበት በኢቱሪ ግዛት መሆኑን የጤና ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በዲአር ኮንጎ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ950 መሻገሩን መገናኛ ብዙኃን የሀገሪቱን ባለሥልጣናት ጠቅሰው ዘግበዋል።
በበሽታው ምክንያት 245 ሰዎች መሞታቸውን የጤና ሚኒስትሩ ሰኔ 12 ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
ቀደም ሲል በእስራኤል የመጀመሪያው በኢቦላ የተጠረጠረ ሰው መገኘቱን መገናኛ ብዙኃን ዘግበው ነበር።
ሩሲያ በሽታውን ለመከላከል የምታደርገውን ድጋፍ የቀጠለች ሲሆን በቅርቡ ከ7,000 በላይ የምርመራ መሣሪያዎችን ለዲአር ኮንጎ፣ ለኮንጎ ሪፐብሊክ እና ለኡጋንዳ ልካለች።
ቪዲዮ፦ ሮጀር ካምባ፣ የጤና ሚኒስትር
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X