ብልጽግና ፓርቲ አብላጫ የፓርላማ ወንበር ማሸነፉን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopiaብልጽግና ፓርቲ አብላጫ የፓርላማ ወንበር ማሸነፉን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ
ብልጽግና ፓርቲ አብላጫ የፓርላማ ወንበር ማሸነፉን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 21.06.2026
ሰብስክራይብ

ብልጽግና ፓርቲ አብላጫ የፓርላማ ወንበር ማሸነፉን ምርጫ ቦርድ አስታወቀ

​ ገዥው ፓርቲ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 ወንበሮችን በማሸነፍ የአብላጫ ድምፅ ያገኘ ሲሆን ተፎካካሪ ፓርቲዎች እና የግል ተወዳዳሪዎች በአጠቃላይ 48 ወንበሮችን እንዳገኙ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሰዓታት በፊት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

​ምክር ቤቱ በአጠቃላይ 547 ወንበሮች ያሉት ሲሆን ከፍተኛ ወንበር ያሸነፈው ፓርቲ መንግሥት መመሥረት ይጠበቅበታል።

​በተጨማሪም ቦርዱ በተመዘገቡ የምርጫ ግድፈቶች ምክንያት በ14 የምርጫ ክልሎች ድጋሚ ምርጫ እንዲካሄድ መወሰኑን ገልጿል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0