በስዊዘርላንድ የተካሄደው የመጀመሪያው ዙር የከፍተኛ ደረጃ የአሜሪካ–ኢራን ድርድር ተጠናቀቀ
19:10 21.06.2026 (የተሻሻለ: 19:14 21.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በስዊዘርላንድ የተካሄደው የመጀመሪያው ዙር የከፍተኛ ደረጃ የአሜሪካ–ኢራን ድርድር ተጠናቀቀ
አሜሪካ፣ ኢራን፣ ፓኪስታን እና ኳታርን ያካተተው የመጀመሪያው ዙር የአራቱ ወገኖች ውይይት መጠናቀቁንና ሁለተኛው ስብሰባ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ይጀመራል ተብሎ እንደሚጠበቅ የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች አመልክተዋል።
ውይይቶቹ ትኩረታቸውን ያደረጉት በሰኔ 11ዱ የኢስላማባድ የመግባቢያ ሰነድ አንቀጽ 13 አፈጻጸም ላይ ነው።
በአንቀጽ 13 መሠረት፤ ስለ መጨረሻው ስምምነት ድርድር መጀመር የሚቻለው በአምስት ቁልፍ ድንጋጌዎች ላይ አፈጻጸም ሲጀመር ብቻ ነው፦
ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ግንባሮች የተኩስ አቁም መታወጅ፣
የአሜሪካ የባሕር ኃይል እገዳ መነሳት፣
የሆርሙዝ ስርጥ ድጋሚ ሲከፈት፣
የኢራን የነዳጅ ወጪ ንግድ ገደብ መንሳት፣ ማቃለያዎች
በእግድ ላይ ያሉ የኢራን ሀብቶችን መልቀቅ።
የዛሬው ቀዳሚ ጉዳይ ወደ ቀጣዩ የድርድር ምዕራፍ ከሚደረገው ሽግግር በፊት የሊባኖስ የተኩስ አቁም ድንጋጌዎች ትግበራን ማረጋገጥ እንደነበር የኢራን ባለሥልጣናት ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X