“ባለፉት ጥቂት ሰዓታት ውስጥ ትልቅ መሻሻል አሳይተናል” ሲሉ ቫንስ ከአሜሪካ–ኢራን ድርድር በፊት ተናገሩ

ሰብስክራይብ

“ባለፉት ጥቂት ሰዓታት ውስጥ ትልቅ መሻሻል አሳይተናል” ሲሉ ቫንስ ከአሜሪካ–ኢራን ድርድር በፊት ተናገሩ

​የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ጄዲ ቫንስ አሜሪካ፣ ኢራን፣ ፓኪስታን እና ኳታርን ያካተተው የአራቱ ወገኖች ውይይት በስዊዘርላንድ ከመጀመሩ አስቀድሞ ቀጣናዊ ግንኙነቶችን ለመለወጥ ሂደቱ ተስፋ ሰጪ እንደሆነ ገልጸዋል።

 

አንኳር የቫንስ ንግግሮች፦

​🟠 አሜሪካ "አዲስ ምዕራፍ ለመክፈት" እና "አሮጌ አካሄዷን" መቀየር ትፍልጋለች፣

​🟠 የቴክኒክ ውይይቶች እያንዳንዱን አለመግባባት ሙሉ በሙሉ ባይፈቱም፤ ሁለቱንም ወገኖች "በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ቡድን" ያገናኛል፣

​🟠 ትራምፕ አሜሪካውያን ተደራዳሪዎች ዲፕሎማሲያዊ መፍትሔ እንዲፈልጉ የፈቀዱ ሲሆን ሁሉን አቀፍ ቀጣናዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ ቁርጠኛ ሆነው እንደቀጠሉ ነው፣

​🟠 የትራምፕ አስተዳደር ይህንን ሂደት የመካከለኛው ምስራቅ ግንኙነቶችን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ በዘላቂነት ለመቀየር እንደ መልካም ዕድል ይመለከተዋል፣

🟠 ቫንስ የሊባኖስን የተኩስ አቁም ስምምነት በማስከበር ረገድ መሻሻሎች መታየታቸውን ጠቅሰው፤ እንዲህ ዓይነቶቹ የተኩስ አቁም ስምምነቶች ብዙ ጊዜ "ውጥንቅጥ እንደሚበዛባቸው" ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0