የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለ2019 በጀት ዓመት ሪከርድ የሆነ 502.27 ቢሊዮን ብር በጀት አቀረበ
16:59 21.06.2026 (የተሻሻለ: 17:04 21.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለ2019 በጀት ዓመት ሪከርድ የሆነ 502.27 ቢሊዮን ብር በጀት አቀረበ
⬆ ይህ በጀት ከ2018 ዓ.ም ጋር ሲነጻጸር የ43 በመቶ ጭማሪ የታየበት ሆኗል።
የበጀት ድልድል እና ምደባው ትኩረቶች፦
የከተማ አስተዳደሩ የልማት ስትራቴጂዎች እና የትኩረት አቅጣጫዎች፣
ድህነት ቅነሳ፣ ዘላቂ የልማት ግቦችን ማረጋገጥ፣ የአገልግሎት አቅርቦት ማሳደግ፣
ማኅበራዊ አገልግሎቶችን ማሻሻል።
ከበጀቱ 71% የሚሆነው ለድህነት ቅነሳና ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ የተመደበ ሲሆን ቀሪው 29% ደግሞ ለአስተዳደራዊ ወጪዎች ተደልድሏል።
የአዲስ አበባ አስተዳደር ካቢኔ በጀቱን አጽድቆ ለከተማው ምክር ቤት መርቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X