የቴህራን እና ዋሽንግተን የመግባቢያ ስምምነት ‘በአብዛኛው የኢራንን ሕዝብ የሚጠቅም ነው’ - ፕሬዚዳንት ፔዜሽኪያን
15:02 21.06.2026 (የተሻሻለ: 15:04 21.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የቴህራን እና ዋሽንግተን የመግባቢያ ስምምነት ‘በአብዛኛው የኢራንን ሕዝብ የሚጠቅም ነው’ - ፕሬዚዳንት ፔዜሽኪያን
የአሜሪካ አቋም “በ180 ዲግሪ ተቀይሯል”፤ ዋሽንግተን ከዚህ በኋላ የኢራንን ጥያቄዎች ችላ ማለት እንደማትችል ገብቷታል ሲሉ መሱድ ፔዜሽኪያን በ33ኛው የገንዘብ እና የባንክ ፖሊሲዎች ኮንፈረንስ ላይ መግለጻቸውን አይአርአይቢ ዘግቧል።
ፕሬዚዳንቱ በተጨማሪ ያነሷቸው ዝርዝሮች ነጥቦች፦
በስዊዘርላንድ የሚካሄደው ንግግር ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለገበያ መስፋፋት እና የቆዩ የኢኮኖሚ ችግሮችን ለመፍታት ዕድሎችን ይከፍታል ብለዋል።
ውይይቱ በኳታር ታግዶ የነበረን 6 ቢሊዮን ዶላር የኢራን ገንዘብ እንዲለቀቅ ያደርጋል ሲሉ ፔዜሽኪያን አክለዋል።
ኢራን የፋይናንስ ሀብቶችን በድጋሚ ማግኘት እንደምትችልና እንዴት መጠቀም እንዳለባትም ራሷ እንደምትወስን ገልጸዋል።
ኢራን ለሰላማዊ ዓላማ የምታከናውነውን የዩራኒየም ማበልጸግ ሥራ እንደማታቆም እና አሜሪካም ይህንን አቋም ለመቀበል እንደተገደደች ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X