የዚምባብዌ አርሶ አደሮች ከዕቅድ በላይ 126,394 ሄክታር መሬት ላይ ስንዴ በመዝራት አዲስ ክብረ ወሰን አስመዘገቡ

ሰብስክራይብ

የዚምባብዌ አርሶ አደሮች ከዕቅድ በላይ 126,394 ሄክታር መሬት ላይ ስንዴ በመዝራት አዲስ ክብረ ወሰን አስመዘገቡ

​ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት፤ የ2026 ምርት በዚህ ዓመት ከተገመተው 662 ሺህ ቶን የላቀ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።

ይህ ስኬት የተመዘገበው ባለፈው ዓመት የተገኘውን የ640,195 ቶን ከፍተኛ የምርት ክብረ ወሰን ተከትሎ ነው።

በግብርና፣ ሜካናይዜሽን እና የውኃ ሀብት ልማት ሚኒስቴር ቋሚ ፀሃፊ ኦበርት ጂሪ፤ “አሁን ትኩረታችን የተሻለ ምርት ለማግኘት በሚያስችሉ የግብርና ተግባራት ማለትም ማዳበሪያ አጠቃቀም፣ የአረም እና የነፍሳት ቁጥጥር እንዲሁም የመስኖ አቅርቦት ላይ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።

​ይህ የምርት ዕድገት የሚከተሉትን ያሳካሉ ተብሎ ይጠበቃል፦

​የዚምባብዌን ከውጭ የሚገባ የስንዴ ወጪ መቅረፍ፣

​ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣

​ የውጭ ምንዛሬን መቆጠብ፣

​ ተጋላጭ የሆኑ ማኅበረሰቦችን ከችግር መጠበቅ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0