የኢትዮጵያ ‘5 ሚሊዮን ኮደሮች’ መርኃ-ግብር የሠልጣኞች ቁጥርን 7 ሚሊዮን ለማድረስ አቅዷል
13:50 21.06.2026 (የተሻሻለ: 13:54 21.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ‘5 ሚሊዮን ኮደሮች’ መርኃ-ግብር የሠልጣኞች ቁጥርን 7 ሚሊዮን ለማድረስ አቅዷል
በፕሮግራሙ በሦስት ዓመት አምስት ሚሊዮን ኮደሮችን ለማሠልጠን ታቅዶ የነበረ ቢሆንም፤ በሁለት ዓመት ውስጥ ብቻ የሠልጣኞች ቁጥር ከአምስት ሚሊዮን በላይ ተሻግሯል።
ከሠልጣኞቹ መካከል ከሦስት ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ሥልጠናውን በስኬት ያጠናቀቁ ሲሆን አሁን ባለው ከፍተኛ መነሳሳት መሠረት እስከ መጪው ነሃሴ ድረስ የሠልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ አዲስ ግብ መቀመጡን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል።
በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የሚደገፈው ይህ መርኃ-ግብር፤ ኢትዮጵያውያንን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የማብቃት ዓላማ ያነገበ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X