የቤኒን–ኒጀር ድንበር ዳግም መከፈት ለሁለቱም ወገን የኢኮኖሚ ዕድል እንደሚፈጥር የኒጀር ባለሙያ ገለጹ

ሰብስክራይብ

የቤኒን–ኒጀር ድንበር ዳግም መከፈት ለሁለቱም ወገን የኢኮኖሚ ዕድል እንደሚፈጥር የኒጀር ባለሙያ ገለጹ

​ እ.ኤ.አ ከ2023 ጀምሮ ተዘግቶ የቆየውን የጋራ ድንበር ዳግም ለመክፈት በኒያሜ እና በኮቶኑ መካከል እየተደረገ ያለው ውይይት፤ ለሁለቱ ሀገራት ጠቃሚ እርምጃ መሆኑን የኒጀር የሲቪል ማኅበረሰብ አንቀሳቃሽ ኤልሀጅ ሳሊሱ አማዱ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

​በከፊል ተቋርጦ የነበረው “የኢኮኖሚ ትርታ” ቀጥሎ፤ “ነገሮች ወደነበሩበት ይመለሳሉ” የሚል ተስፋ እንዳላቸው በመግለጽ፤ በሁሉም ዘርፎች “ሁለቱንም ተጠቃሚ የሚያደርግ” ግንኙነት እንዲኖር ጥሪ አቅርበዋል።

​ ሁለቱ ወገኖች ከተነቃቃ ትብብር ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ያከሉት አማዱ፤ ቀደም ሲል ለነበረው ውጥረት የውጭ ተፅዕኖዎች አስተዋፅኦ አድርገው እንደነበር ጠቁመዋል። ይሁን እንጂ አሁን ዘላቂ መፍትሄ ላይ መድረስ እንደሚቻል መግባባቱ አለ ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0