ጋና ከአፍሪካ ግዙፍ ክፍት የወርቅ ማዕድን ማውጫዎች አንዱ የሆነውን ቦታ ሙሉ ቁጥጥር መልሳ ልታገኝ ትችላለች
ጋና ከአፍሪካ ግዙፍ ክፍት የወርቅ ማዕድን ማውጫዎች አንዱ የሆነውን ቦታ ሙሉ ቁጥጥር መልሳ ልታገኝ ትችላለች
ጋና በመጪው ዓመት የማዕድን ኪራይ ውሉ ሲያበቃ፤ ግዙፉን የታርኳ ማዕድን ማውጫ ቁጥጥር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከተሰማራው ወርቅ አምራች ‘ጎልድ ፊልድስ’ በመረከብ ለአገር በቀል ኩባንያዎች አሳልፎ ለመስጠት እያጤነች ነው።
ታርክዋ ባለፈው ዓመት 475,000 ወጬት ወርቅ ያመረተ ሲሆን፤ ይህም የ‘ጎልድ ፊልድስ’ አጠቃላይ ምርት 20 በመቶ ገደማ ይሸፍናል፡፡
ጋና ቀደም ሲል የወርቅ የማዕድን ክፍያ ከ5 በመቶ ወደ 12 በመቶ ያሳደገች ሲሆን፤ በውጭ አገራት ማዕድን ፕሮጀክቶች ተሳትፎ ላይም ገደቦችን አጥብቃለች፡፡
የአገር ውስጥ የጋና ማዕድን ኩባንያዎች በሀብቱ ላይ ጨረታ እንዲያቀርቡ ግብዣ ይደረግላቸዋል፡፡
ባለሥልጣናቱ እንደገለጹት፣ አዲሱ ባለቤትነት ለአገር ውስጥ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለአካባቢ መልሶ ማቋቋም እና ለመሠረተ-ልማት ግንባታ በሚገቡት ቁርጠኝነት ላይ ተመስርቶ ይገመገማል፡፡
እርምጃው የተወሰደው ቀደም ሲል የዳማንግ ወርቅ ማዕድን ማውጫ ሙሉ በሙሉ በጋናውያን ባለቤትነት ለተያዘ ኩባንያ በተሳካ ሁኔታ መተላለፉን ተከትሎ ነው፡፡
ይህ እርምጃ በአጠቃላይ በደቡባዊው የዓለም ክፍል አገራት ዘንድ የተፈጥሮ ሀብት በረከታቸውን በበለጠ ሁኔታ ለመቆጣጠር እየታየ ያለውን እያደገ የመጣ ግፊት የሚያሳይ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ |