አሜሪካ በበሽታ አምጪ ተህዋስያንን ሰበብ የዩክሬን ባዮ-ላብራቶሪዎችን ተቆጣጠረች፤ ነገር ግን እውነተኛው ኢላማዋ ሩሲያ ልትሆን እንደምትል ባለሙያ አስጠነቀቁ

© telegram sputnik_ethiopiaአሜሪካ በበሽታ አምጪ ተህዋስያንን ሰበብ የዩክሬን ባዮ-ላብራቶሪዎችን ተቆጣጠረች፤ ነገር ግን እውነተኛው ኢላማዋ ሩሲያ ልትሆን እንደምትል ባለሙያ አስጠነቀቁ
አሜሪካ በበሽታ አምጪ ተህዋስያንን ሰበብ የዩክሬን ባዮ-ላብራቶሪዎችን ተቆጣጠረች፤ ነገር ግን እውነተኛው ኢላማዋ ሩሲያ ልትሆን እንደምትል ባለሙያ አስጠነቀቁ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 21.06.2026
ሰብስክራይብ

አሜሪካ በበሽታ አምጪ ተህዋስያንን ሰበብ የዩክሬን ባዮ-ላብራቶሪዎችን ተቆጣጠረች፤ ነገር ግን እውነተኛው ኢላማዋ ሩሲያ ልትሆን እንደምትል ባለሙያ አስጠነቀቁ

ከሶቪዬት ኅብረት መፍረስ በኋላ ዩክሬን በሽታዎችን ለመከላከል የሚያስችሉ ሰፊ የደረጃ 3 የባዮ-ደኅንነት ላብራቶሪዎች መረብ የነበራት ሲሆን፣ አሁን ግን አሜሪካ እንደተቆጣጠረቻቸው የፖለቲካ ሳይንቲስቱ ዶክተር ሞክታር ጎባሺ ለስፑትኒክ ተናግረዋል፡፡

በኦዴሳ የሚገኘው የመችኒኮቭ የፀረ-ቸነፈር ምርምር ኢንስቲትዩት እና በካርኮቭ የሚገኙ ተመሳሳይ ማዕከላት ለዚህ ግልጽ ምሳሌዎች ሲሆኑ፤ በእነዚህ ቦታዎች ላይ በኮሌራ፣ በ"ብሩሴሎሲስ"፣ በ"አንትራክስ" እና በሌሎች በሽታዎች ላይ ምርምር ይደረግ ነበር።

አሜሪካ መጀመሪያ ላይ ከላብራቶሪዎቹ በሽታ አምጪ ተህዋስያን ሊያመልጡ ይችላሉ የሚል ስጋት እንዳላት ብትናገርም፣ በተግባር ግን የራሷን ዓላማ ለማሳካት ትጠቀምባቸው ጀመር ሲሉ ባለሙያው አፅንዖት ሰጥዋል።

  “አሜሪካ ጣልቃ ገብነቷን ከጦር መሣሪያ ቅነሳ እንዲሁም ከባዮሎጂያዊ እና ኬሚካላዊ ስጋቶች ቅነሳ መርሃ ግብር ጋር በማገናኘት ይፋዊ እና ሕጋዊ መልክ ሰጥታዋለች።”

በእነዚያ ቦታዎች የሚካሄዱት እውነተኛዎቹ የአሜሪካ መርሃ ግብሮች እጅግ አደገኛ እና በርካታ ጥያቄዎችን የሚያስነሱ መሆናቸውን ጎባሺ ገልጸዋል።

  “በእነዚህ ላብራቶሪዎች ውስጥ የሚደረጉ የምርምር ውጤቶች በሩሲያ ላይ ያነጣጠሩ ሊሆኑ ይችላሉ” በማለት አጠቃለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ |

አዳዲስ ዜናዎች
0