በጋና የተካሄደው ጉባኤ በአክራ የካሳ ፍትሕ ስትራቴጂን አጸደቀ

በጋና የተካሄደው ጉባኤ በአክራ የካሳ ፍትሕ ስትራቴጂን አጸደቀ
አዲሱ ማዕቀፍ በባርነት፣ በቅኝ ግዛት፣ በዘር ማጥፋት እና በዘር መድልዎ ለተጎዱ አፍሪካውያን እና የአፍሪካ ተወላጆች በሙሉ ፍትሐዊ እና ተመጣጣኝ የካሳ ክፍያን ለማረጋገጥ የሚያስችል ፍኖተ-ካርታ እንደሚያቀርብ የጋና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከስብሰባው በኋላ ገልጿል፡፡
ዋና ዋና ነጥቦች፦
ከባርነት፣ ከቅኝ ግዛት እና ከተያያዙ ታሪካዊ በደሎች ጋር የተያያዙ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎችን ለመፍታት በማለም፤ የዕዳ ሽግሽግ እና ስረዛን ጨምሮ የሀገር ውስጥ የዕዳ ሸክሞችን ለማቅለል የሚያስችሉ ባለብዙ ወገን እርምጃዎች እየታዩ ናቸው፡፡
ውይይቱ የባህል ቅርሶችን፣ የሰዎች ቅሪተ-አካላትን፣ ማህደሮችን እና ሌሎች የቅርስ ቁሳቁሶችን ወደ መነሻ አገራቸው መመለስን ማፋጠንን ያካትታል፡፡
ስብሰባው በተጨማሪም እነዚህን ተነሳሽነቶች ተግባራዊ ለማድረግ እና ክትትል ለመቆጣጠር በርካታ ኮሚሽኖች መቋቋማቸውን አስታውቋል።
የጋናው ፕሬዝዳንት ጆን ማሃማ እንዳሉት፤ ለካሳ ፍትሕ የቀረበው የባለሙያዎች ኮሚሽን ከባሪያ ንግድ ጋር ታሪካዊ ትስስር ያላቸውን የአገራት መሪዎች የሚያካትት ሲሆን፤ ይህም እሳቸውን፣ የባርባዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ ሞትሊን እንዲሁም የላይቤሪያ፣ ናሚቢያ እና ሴኔጋል ፕሬዝዳንቶችን ያካተተ ይሆናል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ |