የታመመች ዶሮውን ይዞ ሆስፒታል የሄደው ታዳጊ እና ርህራሄ የከፈተው የዕድል በር

© telegram sputnik_ethiopiaየታመመች ዶሮውን ይዞ ሆስፒታል የሄደው ታዳጊ እና ርህራሄ የከፈተው የዕድል በር
የታመመች ዶሮውን ይዞ ሆስፒታል የሄደው ታዳጊ እና ርህራሄ የከፈተው የዕድል በር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.06.2026
ሰብስክራይብ

#viral | የታመመች ዶሮውን ይዞ ሆስፒታል የሄደው ታዳጊ እና ርህራሄ የከፈተው የዕድል በር

ታዳጊ ማርቆስ አበባየሁ ያሳደጋት ዶሮ ታማበት ባያስችለው ወደ ደንበጫ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ይዟት አመራ። የጤና ባለሙያው ዑመር ጫኔ፣ ታዳጊውን በመቅረጽ ቪዲዮውንም በማኅበራዊ ሚዲያ አጋርቶ ወደ አንድ ሚሊዮን ገደማ እይታ በማግኘት የብዙዎችን ልብ ሰርቋል።

“ልጁ በወቅቱ ዶሮዋን ይዟት በመምጣቱ ትክክለኛ ቦታ አይደለም በሚል ያንገራገሩት ቢኖሩም፤ ልጁን ሳየው በልጅነት ልቦና መሆኑ እንዲሁም ፊቱ ላይ ያስተዋልኩት የዋህነት ስላሳዘነኝ ቪዲዮውን ልቀርፀው ችያለሁ፡፡" ሲል ዑመር ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግሯል፡፡

አዲሱ ምዕራፍ

የማርቆስን ርህራሄ የተመለከተ አንድ የግል ድርጅት 100 ዶሮዎችን በስጦታ ሊያበረክትለት ቃል ገብቷል። በተጨማሪም ማርቆስንና ዑመርን ወደ አዲስ አበባ በማምጣት፣ በዶሮ እርባታ ዙሪያ የአቅም ግንባታ ሥልጠና እየሰጣቸው ይገኛል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0