የስደተኞች አቀባበል፦ የአፍሪካ አገራት የገቡትን ቃል እያከበሩ ቢሆንም፣ ፈተናዎች ግን አሁንም ቀጥለዋል - የሥነ-ሕዝብ ባለሙያ

ሰብስክራይብ

የስደተኞች አቀባበል፦ የአፍሪካ አገራት የገቡትን ቃል እያከበሩ ቢሆንም፣ ፈተናዎች ግን አሁንም ቀጥለዋል - የሥነ-ሕዝብ ባለሙያ

ዛሬ ሰኔ 13 ቀን የሚከበረውን የዓለም አቀፍ የስደተኞች ቀንን ምክንያት በማድረግ ዣን ፍራንስዋ ሬጂስ ሲንዳይሄቡራ ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት ቃለ-ምልልስ፤ ስደተኞችን ተቀባይ አገራት በመጀመሪያ ደረጃ “የኢኮኖሚ ተፈጥሮ ካላቸው ችግሮች” ጋር እንደሚጋፈጡ ተናግረዋል።

ባለሙያው አፅንዖት ሰጥተው እንደገለጹት፤ ከአገራቸው የተሰደዱ ሰዎችን ሰብዓዊ ክብር የጠበቀ ሕይወት ዋስትና ለመስጠት የሚያስችሉ መሠረተ-ልማቶች በእጅጉ ያስፈልጋሉ።

በመቀጠልም “የሀገር ሉዓላዊነት ጥያቄ” ይነሳል፤ ምክንያቱም በስደተኞቹ መካከል የሽብር ቡድኖች ወይም በየአገራቸው በሕግ የሚፈለጉ ግለሰቦች ሊኖሩ ስለሚችሉ ነው ብለዋል።

ይህንን ለመፍታት የአህጉሪቱ መሪዎች ቀዳሚ ተግባር “ሰላምን ለማረጋገጥ የተቻለውን ሁሉ ማድረግ” መሆን እንዳለበት ሲንዳይሄቡራ አሳስበዋል።

አክለውም፣ “ነገር ግን ከሁሉም አስቀድሞ፣ በስደተኝነት ላይ ያሉ ሰዎችን ለመጠበቅ የሚያስችሉ የሕግ መሣሪያዎችን ማጠናከር ያስፈልጋል” ብለዋል።

ባለሙያው ሲያጠቃልሉ “የመጠለያ ፈላጊዎችን ጥበቃ ሕጋዊ ሥርዓት ለማጠናከር ክልላዊም ሆነ ዓለም አቀፋዊው ማኅበረሰብ በጋራ መንቀሳቀስ አለበት” ሲሉ የሐሳብ ጥቆማቸውን ሰጥተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0