ሩሲያ 7 ሺህ የኢቦላ መመርመሪያ ቁሳቁሶችን ወደ አፍሪካ ላከች - ሮስፖትሬብናድዞር

© telegram sputnik_ethiopiaሩሲያ 7 ሺህ የኢቦላ መመርመሪያ ቁሳቁሶችን ወደ አፍሪካ ላከች - ሮስፖትሬብናድዞር
ሩሲያ 7 ሺህ የኢቦላ መመርመሪያ ቁሳቁሶችን ወደ አፍሪካ ላከች - ሮስፖትሬብናድዞር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.06.2026
ሰብስክራይብ

ሩሲያ 7 ሺህ የኢቦላ መመርመሪያ ቁሳቁሶችን ወደ አፍሪካ ላከች - ሮስፖትሬብናድዞር

የሩሲያ የሸማቾች መብት ጥበቃ እና ሰብዓዊ ደኅንነት ቁጥጥር የፌዴራል አገልግሎት፣ ለዚህ አዲስ የቫይረስ ዝርያ የሚያገለግሉ የፒሲአር መመርመሪያዎችን በአራት ቀናት ውስጥ ብቻ በማልማት እና ምርቱን በማደራጀት በዓለም ቀዳሚው መሆኑን ተቋሙ አስታውቋል።

እነዚህ ለቡንዲቡግዮ የኢቦላ ዝርያ የሚያገለግሉ መመርመሪያዎች ወደሚከተሉት አገራት ተልከዋል፦

ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ

የኮንጎ ሪፐብሊክ

ኡጋንዳ

እንደ ሮስፖትሬብናድዞር ገለጻ፣ መመርመሪያዎቹ በሩሲያ እና በየአገራቱ የሀገር ውስጥ ባለሙያዎች ወረርሽኙ በተቀሰቀሰበት ስፍራ ውጤታማነታቸው የተረጋገጠ ሲሆን ከሌሎች አገራት መመርመሪያዎች ጋር የንፅፅር ፍተሻም ተደርጎባቸዋል

በተጨማሪም ተቋሙ ከ20 በላይ ለሚሆኑ የኡጋንዳ ዜጎች በበሽታ መመርመር እና በወረርሽኝ መከላከል ዙሪያ ሥልጠና ሰጥቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0