ሩዋንዳ በ2030 የተሟላ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በኬፕ ታውን ‘የአፍሪካ ኢነርጂ ፎረም 2026’ ላይ አዳዲስ ባለሀብቶችን እየፈለገች ነው - የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

ሰብስክራይብ

ሩዋንዳ በ2030 የተሟላ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በኬፕ ታውን ‘የአፍሪካ ኢነርጂ ፎረም 2026’ ላይ አዳዲስ ባለሀብቶችን እየፈለገች ነው - የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

አገሪቱ ከጎርጎሮሳውያኑ 1994 ወዲህ ከ85 እስከ 86 በመቶ የሚሆነውን የኤሌክትሪክ ሽፋን ማዳረስ መቻሏን የሩዋንዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦሊቪዬ ጄ.ፒ. ንዱሁንጊሬሄ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ከአፍሪካ ኢነርጂ ፎረም ጎን ለጎን ሚኒስትሩ ከስፑትኒክ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ “ኃይል (ኢነርጂ) በራሱ ዝም ብሎ የሚቆም ነገር እንዳልሆነ እናውቃለን፤ እርሱ ለልማታችን መሣሪያ ነው” ብለዋል።

እያንዳንዱ አገር በራሱ ብቻ ለመልማት “በጣም አነስተኛ” በመሆኑ፤ የአፍሪካን ኢንዱስትራላይዜሽን ለመደገፍና የኃይል ማመንጫ እንዲሁም የማስተላለፊያ ሥራዎችን ለማሳለጥ ቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ትስስር መፍጠር እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0