‘ይህ የውሳኔ ሐሳብ መድረሻ ሳይሆን የ‘ጉዞ’ መጀመሪያ ነው’፦ የአፍሪካ መሪዎች ስለ ታሪካዊ ፍትሕ እና ካሳ ክፍያ

ሰብስክራይብ

‘ይህ የውሳኔ ሐሳብ መድረሻ ሳይሆን የ‘ጉዞ’ መጀመሪያ ነው’፦ የአፍሪካ መሪዎች ስለ ታሪካዊ ፍትሕ እና ካሳ ክፍያ

በጋና አክራ በተካሄደው “የሚቀጥሉት እርምጃዎች” ዓለም አቀፍ የታሪካዊ ፍትሕ እና ካሳ ክፍያ ጉባኤ ላይ፤ የአፍሪካ ፕሬዚዳንቶች የአትላንቲክ ውቅያኖስ የባሪያ ንግድን በሰብዓዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀል አድርጎ የደነገገውን የቅርብ ጊዜውን የተባበሩት መንግሥታት የውሳኔ ሐሳብ ወደ ተግባር ለመለወጥ ጥሪ ማቅረባቸውን የስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ ዘግቧል።

የሴኔጋል ፕሬዚዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ፦

“ይህ የውሳኔ ሐሳብ ተራ ምሳሌያዊ ምልክት ሆኖ መቅረት የለበትም። በማንነት እና በወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ የተመሠረተ አዲስ ጎዳና መክፈት አለበት። ፍትሕ የጋራ ኃላፊነት ነው” ብለዋል። የካሳ ክፍያ ታሪካዊ እውነትን፣ የክብር መመለስን እና የዘረኝነትን ትግል የሚያካትት መሆኑን አጽንኦት በመስጠት፤ ወጣቶችን፣ ከያንያንን (አርቲስቶችን) እና ሲቪል ማኅበረሰቡን ያሳተፉ ተጨባጭ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጥሪ አቅርበዋል።

የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ቦአካይ፦

ይህ ጉባኤ የውሳኔ ሐሳቡ ለእውነት፣ ለፍትሕ፣ ለማገገምና ለተቋማዊ ጥገና ማዕቀፍ መሆኑን ለማረጋገጥ ያለመ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ ትርጉም ያለው የካሳ ክፍያ ከገንዘብ ማዕቀፍ ባለፈ ታሪካዊ እውነትን፣ የማንነት መመለስን እና ተቋማዊ ጥንካሬን ማካተት እንዳለበት አሳስበዋል።

የናሚቢያ ፕሬዚዳንት ኔቱምቦ ናንዲ-ንዳይትዋ፦

የውሳኔ ሐሳቡን እንደ አንድ ትልቅ ምዕራፍ የገለጹት ቢሆንም፤ መድረሻ ሳይሆን ወደ እውነት፣ ዕውቅና መስጠት፣ ማገገም እና ፍትሕ የሚመራ የጉዞ መጀመሪያ መሆኑን ጠቅሰዋል። እውነተኛ እርቅ የሚጀምረው ሰዎች የራሳቸውን ታሪክ እንዲናገሩ ሲፈቀድላቸው እና ታሪካቸውም በሐቀኝነት ተቀባይነት ሲያገኝ ነው ሲሉ አክለዋል።

  የጋና ፕሬዚዳንት ጆን ድራማኒ ማሃማ፦

“እዚህ የተሰበሰብነው ስለ ቀደመው ታሪክ ለመወያየት ብቻ ሳይሆን፤ በሕዝባችን ላይ እስካሁን ከተፈጸሙት ታላላቅ ወንጀሎች መካከል አንዱ ለሆነው ድርጊት የሰው ልጅ ምን ዓይነት ምላሽ እንደሚሰጥ ለመወሰን ጭምር ነው” ብለዋል። ይህ ትውልድ መርከቦቹን ባይገነባም ወይም የእርሻ ቦታዎቹን ባያስተዳድርም “እያንዳንዱ ትውልድ ከባለፈው ታሪክ ኃላፊነቶችን ይወርሳል” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0