የአፍሪካውያን ተቃውሞ የጀመረው በተባበሩት መንግሥታት ሳይሆን በእርሻ ቦታዎች ላይ ነው ሲሉ የካሪኮም የካሳ ክፍያ ኮሚሽን ሰብሳቢ ተናገሩ

ሰብስክራይብ

የአፍሪካውያን ተቃውሞ የጀመረው በተባበሩት መንግሥታት ሳይሆን በእርሻ ቦታዎች ላይ ነው ሲሉ የካሪኮም  የካሳ ክፍያ ኮሚሽን ሰብሳቢ ተናገሩ

በአክራው የካሳ ክፍያ ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ፕሮፌሰር ሰር ሂላሪ ቤክልስ፤ በፈረንጆቹ 1675 በባርባዶስ የነበሩት የመጀመሪያው ትውልድ ጋናውያን በባርነት ላይ አመጽ አቀጣጥለው እንደነበርና አመፁ በ1679 ሲገታ 25 ያህሉ በሕይወት እያሉ መቃጠላቸውን አስታውሰዋል።

ቤክልስ ለታዳሚው ሲያስረዱ “በባርነት የተጫኑ አፍሪካውያንን በአትላንቲክ ውቅያኖስ ያሻገሩ 40 በመቶ የሚሆኑት መርከቦች በሙሉ አመጽ አስተናግደዋል” ብለዋል። “ተቃውሞው የጀመረው እዚሁ ነው። በባሪያ መርከቦች ላይም ቀጥሏል። በቅኝ ግዛቶችም ውስጥ ቢሆን አልቆመም።”

ከ80 በላይ አገራት የተወከሉበት ይህ ጉባኤ፤ የአትላንቲክ ውቅያኖስ የባሪያ ንግድን በሰብዓዊነት ላይ የተፈጸመ እጅግ አሰቃቂ ወንጀል መሆኑን የሚያውጀውን የተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ የመጋቢት ውሳኔ ሐሳብ ተከትሎ የተዘጋጀ ነው።

ቤክልስ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የውሳኔ ሐሳብ የ“ዓለም አቀፍ አፍሪካዊ ንቃተ ህሊና” እና የዘመናት ፅናት ውጤት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

በመጨረሻም፣ ወደ አፍሪካ “የመመለሻ በር” መመለስን፤ የ21ኛውን ክፍለ ዘመን ቅርጽ በሚያስይዘውና በዓለም አቀፍ ደረጃ የታሪካዊ ፍትሕን ለማስፈን በተቀረጸው ባለ 10 ነጥብ ዕቅድ ውስጥ እንደ አንድ አካል አድርጎ ዓለም እንዲመለከተው አሳስበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0