አፍሪካ ለታሪካዊ ካሳ ጥያቄ የማይበገር ግንባር መፍጠር አለባት - የጋና ባለሥልጣን

ሰብስክራይብ

አፍሪካ ለታሪካዊ ካሳ ጥያቄ የማይበገር ግንባር መፍጠር አለባት - የጋና ባለሥልጣን

አፍሪካውያን አገራት በቅኝ ግዛት ዘመን በሰብዓዊነት ላይ ለተፈጸሙ ወንጀሎች የሚጠየቀውን የካሳ፣ የቅርሶች መመለስ እና የተገቢ ክፍያዎች ጥያቄ ወደፊት ለማስቀጠል፤ በጉዳዩ ላይ የተዋሃደ አቋም መያዝ እንዳለባቸው በካሪቢያን ቀጣና የጋና ልዩ መልዕክተኛ ክዋሲ ኪዬ ዳርክዋህ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በጋና መዲና አክራ በተካሄደው የባርነት ዘመን የካሳ ክፍያ ጉባኤ ጎን ለጎን መልዕክተኛው ሲናገሩ፤ “አንድነታችንን ካላጠናከርን ልክ እንደ አፍሪካ መጥረጊያ እያንዳንዳችን በቀላሉ ተነጥለን ልንሰበር እንችላለን” ሲሉ ገልጸዋል።

እንደ ልዩ መልዕክተኛው ገልጻ፤ በተባበሩት መንግሥታት የባሪያ ንግድን በተመለከተ የጸደቀው የውሳኔ ሐሳብ፣ ሦስት አገራት ብቻ የተቃወሙት መሆኑ የፍትሕ ጥያቄው የማይቀለበስ ከፍተኛ መነቃቃት እያገኘ መምጣቱን ያሳያል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0