ሩሲያ እና ኬንያ የወንጀል መከላከል አጋርነት እና የዓቃቤ ሕግ ትብብር ለመመሥረት ተስማሙ

ሰብስክራይብ

ሩሲያ እና ኬንያ የወንጀል መከላከል አጋርነት እና የዓቃቤ ሕግ ትብብር ለመመሥረት ተስማሙ

በሩሲያ ዋና ዓቃቤ ሕግ አሌክሳንደር ጉትሳን እና በኬንያ የሕዝብ ክስ ዳይሬክተር ሬንሰን ሙሌሌ ኢንጎንጋ መካከል በተደረገው ስብሰባ፤ ሁለቱ ወገኖች በወንጀል መከላከል እና በሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ላይ የሚያተኩር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ በተለይ በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ያተኩራል፦

▪ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን መዋጋት፣

▪ የወንጀል ሀብት እና ንብረቶችን ማስመለስ።

ሩሲያ የታዛቢነት ማዕረግ ያገኘችበት ‘የምሥራቅ አፍሪካ የንብረት ማስመለስ የጋራ መረብ’ ለዚህ ሥራ ጠቃሚ መሣሪያ መሆኑን አሌክሳንደር ጉትሳን ገልጸዋል።

ሁለቱ ወገኖች በሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ማዕቀፍ እና በሩሲያ ዋና ዓቃቤ ሕግ ቢሮ ዩኒቨርሲቲ በሚሰጡ የስልጠና መርሃ ግብሮች አማካኝነት ትብብራቸውን ለማስፋፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0