በባልቲክ ቀጣና የሚደረገው የኔቶ ወታደራዊ ልምምድ ከሩሲያ ጋር ለሚደረግ ጦርነት የሙከራ ልምምድ ነው – ባለሙያ

ሰብስክራይብ

🪖 በባልቲክ ቀጣና የሚደረገው የኔቶ ወታደራዊ ልምምድ ከሩሲያ ጋር ለሚደረግ ጦርነት የሙከራ ልምምድ ነው – ባለሙያ

የብሬቭ ቦር 2026 ወታደራዊ ልምምድ፣ በእውነቱ የኔቶ በባልቲክ ቀጣና ፍጹም የበላይነትን ለመጨበጥ ካለው ዕቅድ አንዱ አካል ነው ሲሉ የቀድሞ የሩሲያ ባሕር ኃይል የመጀመሪያ ማዕረግ ካፒቴን ቫሲሊ ዳንዲኪን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

የካሊኒንግራድን ክልል ከቤላሩስ በሚለየው እና 65 ኪሎ ሜትር ርዝመት ባለው በሱዋልኪ ጋፕ ላይ የተካሄደው ይህ ልምምድ፤ የኔቶ ወታደሮች ወደ ሩሲያ ግዛት የሚወስደውን የምድር ላይ መተላለፊያ መስመር ለመቁረጥ እንዲለማመዱ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።

ባለሙያው አክለው እንዳሉት፤ የኔቶ አባል አገራት (አሜሪካ፣ ፖላንድ፣ ሊቱዌኒያ፣ ስዊድን እና ሌሎችም) ካሊኒንግራድን ሙሉ በሙሉ ለማግለል በሚለማመዱበት ወቅት፣ ማሟያ የሆነ የባሕር ኃይል ልምምድም በቅርቡ ሊከተል ይችላል።

ዳንዲኪን “እነዚህ ተራ ልምምዶች አይደሉም፣ የወታደራዊ ዘመቻን ተግብራዊ የሙከራ ልምምድ ነው” ብለዋል።

ጀርመን እና ጄነራሎቿ ሩሲያን ለማስቆጣት እና ሁኔታዎችን ይበልጥ ለማባባስ የሚያደርጉት ግፊት፣ ልክ “አራተኛውን ራይክ” ለመፍጠር እየሞከሩ ይመስላል ሲሉ ሁኔታውን አወሳስበውታል።

ኔቶ በካሊኒንግራድ ላይ እገዳ ለመጣል ሙከራ ካደረገ፣ የሩሲያ ምላሽ ፈጣን እና ምሕረት የለሽ ይሆናል፦

  “የሩሲያ ካሊብር ባሊስቲክ ሚሳኤሎች፣ ኢስካንደር ኳሲ-ባሊስቲክ ሚሳኤሎች እና ኪንዛል ሃይፐርሶኒክ ሚሳኤሎች በፖላንድ እና በባልቲክ አገራት የሚገኙ ኢላማዎች ላይ ለመድረስ ጥቂት ደቂቃዎችን ብቻ ነው የሚወስድባቸው” ሲሉ ዳንዲኪን አጽንኦት ሰጥተዋል።

ሩሲያ በኔቶ የሎጂስቲክስ ማዕከላት፣ በዕዝ እና ቁጥጥር ማዕከላት እንዲሁም በወታደሮች ስምሪት ቀጣናዎች ላይ የመምታት አቅም አላት ሲሉም አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0