በ2026 ከፍተኛ የጤና አጠባበቅ ደረጃ ያላቸው ቀዳሚ አምስት የአፍሪካ አገራት

በ2026 ከፍተኛ የጤና አጠባበቅ ደረጃ ያላቸው ቀዳሚ አምስት የአፍሪካ አገራት
የጤና አጠባበቅ የአንድን አገር የጤና ሥርዓት ብቃት፣ ተደራሽነት እና ጥንካሬ የሚያንጸባርቅ በመሆኑ ለኑሮ ጥራት ወሳኝ ማሳያ ነው።
እነዚህን ሥርዓቶች ለመገምገም፣ ‘ኑምቢዮ’ የተባለው የኑሮ ጥራት መረጃ ቋት እንደ የሕክምና ባለሙያዎች፣ መሣሪያዎች፣ ሠራተኞች፣ ሐኪሞች እና ወጪዎች ያሉ ቁልፍ ሁኔታዎችን መዝኗል።
ከፍተኛ የጤና አጠባበቅ መለኪያ ያላቸው አምስት የአፍሪካ አገራት የሚከተሉት ናቸው፦
1⃣ ደቡብ አፍሪካ (64.0) በዝርዝሩ ውስጥ ካሉ ሌሎች አገራት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ተደራሽነት እና የአገልግሎት ጥራት አላት፤
2⃣ ኬንያ (62.2) በሕዝብ ጤና ተቋማት ላይ ቀጣይነት ያለው ማሻሻያ በማድረግ የጤና አጠባበቅ አሰጣጥ ሥርዓትን እያገነባች ትገኛለች፤
3⃣ ጋና (57.0) በአሁኑ ወቅት በቂ አገልግሎት ላላገኙ የአገሪቱ አካባቢዎች ዜጎች የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን እያሳደገች ነው፤
4⃣ ቱኒዚያ (56.6) በሕዝብ ጤና ረገድ ጠንካራ አፈጻጸም እያሳየች ቢሆንም፣ በአንዳንድ ማኅበረሰቦች ዘንድ አሁንም ከአቅም እና ከተደራሽነት ጋር በተያያዘ ፈተናዎች ይገጥሟታል፤
5⃣ አልጄሪያ (54.5) በመላው አህጉሪቱ የመድኃኒቶች እና የክትባቶችን ዋጋ ተመጣጣኝ ለማድረግ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት ጋር ያለውን የመድኃኒት ዘርፍ ትብብር እያጠናከረች ነው።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X