የሳኅል ሀገራት ጥምረት ያልተቀነባበረ ጥጥ፣ ወርቅ እና ዩራኒየም ወደ ውጭ መላክ ማቆም አለባቸው - የቡርኪና ፋሶ ጠቅላይ ሚኒስትር

ሰብስክራይብ

የሳኅል ሀገራት ጥምረት ያልተቀነባበረ ጥጥ፣ ወርቅ እና ዩራኒየም ወደ ውጭ መላክ ማቆም አለባቸው - የቡርኪና ፋሶ ጠቅላይ ሚኒስትር

​የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪን ማስፋፋትና ንግድን ማጠናከር የኢኮኖሚ ነፃነት ዋነኛ አንቀሳቃሾች እንዲሁም የሳኅል ጥምረትን ኢኮኖሚ ለመቀየር ዋና ምሰሶዎች መሆን አለባቸው ሲሉ ሪምታልባ ዣን ኢማኑኤል ኡዌድራኦጎ በኡጋዱጉ በተካሄደው የጥምረቱ የኢንዱስትሪ፣ ንግድና የግል ዘርፍ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ገልጸዋል።

ይህንን ለውጥ እውን ለማድረግም የጥምረቱ  አባል ሀገራት የሚከተሉትን ተግባራት ማከናወን እንዳለባቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል፦

በአባል ሀገራቱ መካከል ያለውን የእርስበርስ ንግድ ማሳለጥ፣

ሕገ-ወጥ የንግድ ማጭበርበርን በቁርጠኝነት መዋጋት፣

ፍትሐዊ ያልሆነ የንግድ ውድድርን መከላከል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0