የኢራን እና የአሜሪካ ንግግር በዚህ ሳምንት ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ እንደሚሸጋገር የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስታወቁ
15:00 16.06.2026 (የተሻሻለ: 15:04 16.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢራን እና የአሜሪካ ንግግር በዚህ ሳምንት ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ እንደሚሸጋገር የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አስታወቁ
ዓርብ ዕለት በስዊዘርላንድ የሚጀመረው አዲስ ድርድር ከዋሽንግተን ጋር የሚደረገው ሁለተኛ ምዕራፍ ንግግር መጀመሪያ መሆኑን አባስ አራጋቺ በቴህራን ለሚገኙ ዲፕሎማቶች ገልጸዋል።
አራጋቺ በመግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ጦርነቱን ማቆም፣ የሆርሙዝ ወሽመጥ ጉዳይ እና የታገዱ የኢራን ንብረቶችን መልቀቅ ያካተተው የመጀመሪያው ምዕራፍ አስቀድሞ ተጠናቋል።
በቅርቡ የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ከፊታችን ዓርብ ጀምሮ በይፋ ትግበራ ላይ ይውላል።
ሁለተኛው ምዕራፍ ለ60 ቀናት የሚቆይ ሲሆን ትኩረቱንም በኢራን የኒውክሌር መርኃ-ግብር እና ማዕቀቦችን ማንሳት ላይ ያደርጋል።
ስምምነቱ ከተጠናቀቀበት በቴህራን አቆጣጠር ሰኞ ጠዋት ጀምሮ ጦርነቱ እንዳበቃ መታወጁን አራጋቺ ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X