ሩሲያ የመጀመሪያውን የወይን ምርት ወደ ናይጄሪያ በመላክ የግብርና ገበያ ተደራሽነቷን አሰፋች - አግሮኤክስፖርት

ሰብስክራይብ

ሩሲያ የመጀመሪያውን የወይን ምርት ወደ ናይጄሪያ በመላክ የግብርና ገበያ ተደራሽነቷን አሰፋች - አግሮኤክስፖርት

​ ሩሲያ እ.አ.አ በ2026 የመጀመሪያዎቹ አምስት ወራት፤ ከ48 ቶን በላይ ወይን ለናይጄሪያ መላኳን የሀገሪቱ የግብርና ምርቶች ወጪ ንግድ ልማት ማዕከል አስታውቋል።

​ጭነቱ 24 ቶን የሚያብረቀርቅ ወይን እና ወደ 24 ቶን የሚጠጋ ሌላ ከወይን ፍሬ የተመረተ ወይንን አካቷል።

​ ማዕከሉ አክሎ እንደገለጸው፣ ሩሲያ በተጠቀሰው ተመሳሳይ ጊዜ በአጠቃላይ ከ96 ሚሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸው 397 ሺህ ቶን የግብርና ምርቶችን ወደ ናይጄሪያ ልካለች።

​ይህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የንግድ ትስስር ከተለመዱት ምርቶች ባለፈ፤ ወደ ተለያዩ ዘርፎች እያደገ እና እየሰፋ መምጣቱን የሚያሳይ መሆኑን አግሮኤክስፖርት አመልክቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0