ሩሲያ የመጀመሪያውን የወይን ምርት ወደ ናይጄሪያ በመላክ የግብርና ገበያ ተደራሽነቷን አሰፋች - አግሮኤክስፖርት
12:21 16.06.2026 (የተሻሻለ: 12:24 16.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሩሲያ የመጀመሪያውን የወይን ምርት ወደ ናይጄሪያ በመላክ የግብርና ገበያ ተደራሽነቷን አሰፋች - አግሮኤክስፖርት
ሩሲያ እ.አ.አ በ2026 የመጀመሪያዎቹ አምስት ወራት፤ ከ48 ቶን በላይ ወይን ለናይጄሪያ መላኳን የሀገሪቱ የግብርና ምርቶች ወጪ ንግድ ልማት ማዕከል አስታውቋል።
ጭነቱ 24 ቶን የሚያብረቀርቅ ወይን እና ወደ 24 ቶን የሚጠጋ ሌላ ከወይን ፍሬ የተመረተ ወይንን አካቷል።
ማዕከሉ አክሎ እንደገለጸው፣ ሩሲያ በተጠቀሰው ተመሳሳይ ጊዜ በአጠቃላይ ከ96 ሚሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸው 397 ሺህ ቶን የግብርና ምርቶችን ወደ ናይጄሪያ ልካለች።
ይህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የንግድ ትስስር ከተለመዱት ምርቶች ባለፈ፤ ወደ ተለያዩ ዘርፎች እያደገ እና እየሰፋ መምጣቱን የሚያሳይ መሆኑን አግሮኤክስፖርት አመልክቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X