https://amh.sputniknews.africa/20260616/4338583.html
ጋና እና ኮትዲቯር የኮኮዋ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማጠናከር መግባባት ላይ ደረሱ
ጋና እና ኮትዲቯር የኮኮዋ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማጠናከር መግባባት ላይ ደረሱ
Sputnik አፍሪካ
ጋና እና ኮትዲቯር የኮኮዋ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማጠናከር መግባባት ላይ ደረሱ ሁለቱ ሀገራት የዘርፉን አቅም እና የአርሶ አደሮች ትርፋማነት ለማሳደግ ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ፤ የጋራ የኮኮዋ ጥምረታቸውን 7ኛ የአመራር ኮሚቴ ስብሰባ... 16.06.2026, Sputnik አፍሪካ
2026-06-16T11:56+0300
2026-06-16T11:56+0300
2026-06-16T12:04+0300
sputnik africa
telegram sputnik_ethiopia
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07ea/06/10/4338430_0:219:360:422_1920x0_80_0_0_5f53ac91c5a8dc92c82784ece390c1a8.jpg
ጋና እና ኮትዲቯር የኮኮዋ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማጠናከር መግባባት ላይ ደረሱ ሁለቱ ሀገራት የዘርፉን አቅም እና የአርሶ አደሮች ትርፋማነት ለማሳደግ ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ፤ የጋራ የኮኮዋ ጥምረታቸውን 7ኛ የአመራር ኮሚቴ ስብሰባ በአቢጃን ከፍተዋል። የኮትዲቯር የግብርና ሚኒስትር ብሩኖ ናባኜ ኮኔ፤ አርሶ አደሮች ተገቢውን ገቢ እንዲያገኙ ለማረጋገጥ የተጣጣመ/ወጥ የሆነ የዋጋ አሰጣጥ እንደሚያስፈልግ አጽንዖት ሰጥተዋል። "ዋጋን በማጣጣም ተገቢውን ገቢ እና ፍትሕን ማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ ነው። ኮኮዋ ከምንም በላይ ለአርሶ አደሮች የተሻለ የኑሮ ደረጃ ዋስትና መስጠት አለበት" ሲሉ ተናግረዋል። ተነሳሽነቱ የሁለትዮሽ ትብብርን ለማጠናከር፣ የኑሮ ደረጃን ለማሻሻል እና ይበልጥ ዘላቂ ለሆነ የኮኮዋ ምርት ተጨባጭ ምክረ ሀሳቦችን ለማዘጋጀት ያለመ ነው። "በዓለም ቀዳሚ የኮኮዋ አምራች የሆኑ ሁለት ሀገራት እንደመሆናችን መጠን፤ ኢኮኖሚያችንን ለመጠበቅ በተከታታይ እና ስልታዊ በሆነ መንገድ መንቀሳቀስ አለብን" ያሉት የጋና የገንዘብ ሚኒስትር ካሲየል አቶ ፎርሰን፤ ይህ አቀራረብ ሁለቱ ሀገራት መስተጓጎሎች ሲፈጠሩ ዝም ብሎ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ፤ ተግዳሮቶችን አስቀድመው እንዲገምቱ፣ ድንገተኛ አደጋዎችን እንዲያቃልሉ እና የዘርፉን የወደፊት ዕጣ ፈንታ እንዲቀርጹ እንደሚረዳቸው ገልጸዋል። ከማኅበራዊ የትስስር ገፅ የተገኘ ቪዲዮበእንግሊዘኛ ያንብቡ ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
2026
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
ጋና እና ኮትዲቯር የኮኮዋ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማጠናከር መግባባት ላይ ደረሱ
Sputnik አፍሪካ
ጋና እና ኮትዲቯር የኮኮዋ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማጠናከር መግባባት ላይ ደረሱ
2026-06-16T11:56+0300
true
PT1S
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07ea/06/10/4338430_0:185:360:455_1920x0_80_0_0_f0c6d2734c2f0456428f1d0125f52beb.jpgSputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
sputnik africa, telegram sputnik_ethiopia
sputnik africa, telegram sputnik_ethiopia
ጋና እና ኮትዲቯር የኮኮዋ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማጠናከር መግባባት ላይ ደረሱ
11:56 16.06.2026 (የተሻሻለ: 12:04 16.06.2026) ጋና እና ኮትዲቯር የኮኮዋ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማጠናከር መግባባት ላይ ደረሱ
ሁለቱ ሀገራት የዘርፉን አቅም እና የአርሶ አደሮች ትርፋማነት ለማሳደግ ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ በማቅረብ፤ የጋራ የኮኮዋ ጥምረታቸውን 7ኛ የአመራር ኮሚቴ ስብሰባ በአቢጃን ከፍተዋል።
የኮትዲቯር የግብርና ሚኒስትር ብሩኖ ናባኜ ኮኔ፤ አርሶ አደሮች ተገቢውን ገቢ እንዲያገኙ ለማረጋገጥ የተጣጣመ/ወጥ የሆነ የዋጋ አሰጣጥ እንደሚያስፈልግ አጽንዖት ሰጥተዋል።
"ዋጋን በማጣጣም ተገቢውን ገቢ እና ፍትሕን ማረጋገጥ ወሳኝ ጉዳይ ነው። ኮኮዋ ከምንም በላይ ለአርሶ አደሮች የተሻለ የኑሮ ደረጃ ዋስትና መስጠት አለበት" ሲሉ ተናግረዋል።
ተነሳሽነቱ የሁለትዮሽ ትብብርን ለማጠናከር፣ የኑሮ ደረጃን ለማሻሻል እና ይበልጥ ዘላቂ ለሆነ የኮኮዋ ምርት ተጨባጭ ምክረ ሀሳቦችን ለማዘጋጀት ያለመ ነው።
"በዓለም ቀዳሚ የኮኮዋ አምራች የሆኑ ሁለት ሀገራት እንደመሆናችን መጠን፤ ኢኮኖሚያችንን ለመጠበቅ በተከታታይ እና ስልታዊ በሆነ መንገድ መንቀሳቀስ አለብን" ያሉት የጋና የገንዘብ ሚኒስትር ካሲየል አቶ ፎርሰን፤ ይህ አቀራረብ ሁለቱ ሀገራት መስተጓጎሎች ሲፈጠሩ ዝም ብሎ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ፤ ተግዳሮቶችን አስቀድመው እንዲገምቱ፣ ድንገተኛ አደጋዎችን እንዲያቃልሉ እና የዘርፉን የወደፊት ዕጣ ፈንታ እንዲቀርጹ እንደሚረዳቸው ገልጸዋል።
ከማኅበራዊ የትስስር ገፅ የተገኘ ቪዲዮ
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X