የሆርሙዝ ወሽመጥ የባሕር ትራንስፖርትን ሙሉ በሙሉ ወደ ነበረበት ለመመለስ ከ1 እስከ 3 ወራት ሊወስድ እንደሚችል ግብጻዊ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ገለጹ

ሰብስክራይብ

የሆርሙዝ ወሽመጥ የባሕር ትራንስፖርትን ሙሉ በሙሉ ወደ ነበረበት ለመመለስ ከ1 እስከ 3 ወራት ሊወስድ እንደሚችል ግብጻዊ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ገለጹ

​ በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል መደበኛ የባሕር ጉዞ እንደገና መጀመር በቀጣይነት የባሕር ደህንነትን በማረጋገጥ እና በዓለም አቀፍ ላኪዎች እንዲሁም በኢንሹራንስ ኩባንያዎች መካከል እምነትን መልሶ በመገንባት ላይ የተመሠረተ መሆኑን አህመድ ኤል-ሻሚ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

 

ምቹ ሁኔታ፦ በመሠረተ ልማት ላይ ጉዳት ወይም የባሕር ፈንጂዎች ከሌሉ፤ የመርከብ እንቅስቃሴ በጥቂት ቀናት ውስጥ ቀስ በቀስ ሊቀጥል ይችላል። ነገር ግን ገበያዎች እና የጭነት መርከብ መስመሮች ከቀውሱ በፊት ወደነበረው የሥራ እንቅስቃሴ ለመመለስ ከበርካታ ሳምንታት እስከ ወራት ሊፈጅባቸው ይችላል ብለዋል።

እጅግ የከፋ ሁኔታ፦ ፈንጂዎች ወይም ፈንጂ ሊሆኑ የሚችሉ ቁሶች ከተገኙ፣ ፈንጂዎችን የማጽዳት ሥራ እንደ ስጋቱ ስፋት እና እንደ ዓለም አቀፋዊ ትብብር ደረጃ ሳምንታትን ወይም ወራትን ሊወስድ ይችላል።

በወጪዎች ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ፦ መስመሩ በይፋ መከፈቱን የሚገልጽ ይፋዊ ማስታወቂያ፤ የወጪ ስጋት አረቦንን እና የጦርነት ኢንሹራንስ ወጪዎችን ወዲያውኑ እንደሚቀንስ፤ ይህም የነዳጅ ገበያውን ስጋት እንደሚያቃልል ኤል-ሻሚ አፅንዖት ሰጥተዋል።

​ ሆኖም በዓለም ላይ በባሕር ከሚጓጓዘው ነዳጅ ውስጥ 20% ገደማ የሚተላለፍበትን የአቅርቦት ሰንሰለት ሙሉ በሙሉ ወደ ነበረበት መመለስ፤ በክልሉ ካሉ ቀሪ ስጋቶች ጋር ተያይዞ ከአንድ እስከ ሦስት ወራት ሊወስድ ይችላል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0