አሜሪካ ለራሷ፣ ለእስራኤል እና ለቀጣናው ስትል ከኢራን ጋር በተደረሰው ስምምነት መገዛት ይበጃታል - ኢትዮጵያዊ ባለሙያ
10:10 16.06.2026 (የተሻሻለ: 10:14 16.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
አሜሪካ ለራሷ፣ ለእስራኤል እና ለቀጣናው ስትል ከኢራን ጋር በተደረሰው ስምምነት መገዛት ይበጃታል - ኢትዮጵያዊ ባለሙያ
ግጭቱ ኢራን ኃይሏን ያሳያችበት እና አሜሪካ እስራኤልን እየደገፈች መቀጠሏ ከፖለቲካ እና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራው አንጻር እንደማያዋጣ የተገነዘበችበት ነው ብለው እንደሚያምኑ፤ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ተመራማሪው ዳዊት መዝገበ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልፀዋል።
ዞሮ ዞሮ ግን የስምምነቱ እውነተኛ ውጤት የሚለካው በምዕራብ እስያ ተኩስ መሰማቱ ሲያቆም፣ እስራኤልም ምዕራብ ሊባኖስን ለቃ ስትወጣ እና ከሆርሙዝ ሰርጥ መከፈት ጋር ተያይዞ የዓለም ኢኮኖሚያ ሲረጋጋ እንደሆነ ባለሙያው አብራርተዋል።
“ኢራናውያን ጥብቅ ቅደመ ሁኔታዎችን አስቀምጠዋል። አሜሪካውያኑ ይህንን እንደሚያውቁ እና ይገዙበታልም ብዬ አስባለሁ። አሁን ባለው ሁኔታ ከቀጠለ ይህ ስምምነት ሊሠራ ይችላል።”
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X