ታንዛኒያ አነስተኛ የማዕድን ቁፋሮን ለማበረታታት የማዕድን ምርምር ፈንድ ልታቋቁም ነው
17:28 15.06.2026 (የተሻሻለ: 17:34 15.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ታንዛኒያ አነስተኛ የማዕድን ቁፋሮን ለማበረታታት የማዕድን ምርምር ፈንድ ልታቋቁም ነው
ታንዛኒያ አነስተኛ የማዕድን ቁፋሮን በአብዛኛው በግምት ከሚመራ አሠራር ወደ መረጃ-ተኮር ኢንዱስትሪ ለመቀየር፤ ከጠቅላላ የማዕድን ገቢዋ 10% አዲስ በሚቋቋመው የማዕድን ምርምር ፈንድ ውስጥ እንደምታስገባ የማዕድን ሚኒስትሩ አንቶኒ ማቩንዴ ተናግረዋል።
ይህ እቅድ የ2026/27 በጀት አካል ነው።
መፍትሔ የሚሹ ተግዳሮቶች፦ ይህ ፈንድ አነስተኛ ማዕድን አውጪዎች ለረጅም ጊዜ ሲገጥሟቸው የነበሩ ችግሮችን ዒላማ ያደርጋል፤ ከነዚህም ውስጥ፦
ውስን የሥነ-ምድር መረጃ፣
የካፒታል አቅርቦት እጥረት፣
ጊዜ ያለፈበት ቴክኖሎጂ፣
ተመጣጣኝ የፋይናንስ አቅርቦት ለማግኘት የሚያጋጥሙ ችግሮች ይገኙበታል።
ለምን አስፈለገ፦
አነስተኛ የማዕድን ቁፋሮ ከማዕድን ዘርፍ ከሚገኘው ገቢ ውስጥ 40% ያህሉን የሚያመነጭ ቢሆንም፤ አሁንም ለከፍተኛ ስጋት እና አነስተኛ ምርታማነት የተጋለጠ እንደሆነ ማቩንዴ ገልጸዋል። መንግሥት ማዕድን አውጪዎች ሳይንሳዊ መረጃዎችን፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን እና የተጠና የንግድ ዕቅድን እንዲተገብሩ ይፈልጋል ሲሉም አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X