የሩሲያ ቢኬ-16ኢ ጀልባዎች በአፍሪካ የፀረ-ሽብር ዘመቻዎች ላይ በከፍተኛ ብቃት እያገለግሉ እንደሆነ አምራቹ ገለጸ

© telegram sputnik_ethiopiaየሩሲያ ቢኬ-16ኢ ጀልባዎች በአፍሪካ የፀረ-ሽብር ዘመቻዎች ላይ በከፍተኛ ብቃት እያገለግሉ እንደሆነ አምራቹ ገለጸ
የሩሲያ ቢኬ-16ኢ ጀልባዎች በአፍሪካ የፀረ-ሽብር ዘመቻዎች ላይ በከፍተኛ ብቃት እያገለግሉ እንደሆነ አምራቹ ገለጸ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 15.06.2026
ሰብስክራይብ

የሩሲያ ቢኬ-16ኢ ጀልባዎች በአፍሪካ የፀረ-ሽብር ዘመቻዎች ላይ በከፍተኛ ብቃት እያገለግሉ እንደሆነ አምራቹ ገለጸ

ግዙፉ የሩሲያ የአነስተኛ ጦር መሣሪያ አምራች ካላሽኒኮቭ፤ በዚህ ዓመት ሁለት የቢኬ-16ኢ ፈጣን የጥቃት ጀልባዎችን ለአንድ የአፍሪካ ደንበኛ ማድረሱንና ተጨማሪ አምስት ጀልባዎችን እየገነባ መሆኑን ገልጿል። ጀልባዎቹ በፀረ-ሽብር ዘመቻዎች ላይ ባሳዩት አፈጻጸም አዎንታዊ ግብረመልስ እንደተሰጣቸው የኩባንያው ተወካይ ለሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።

 

የቢኬ-16ኢ ጀልባዎች ዋና ዋና ባህሪያት፦

በባሕር ዳርቻዎች ለሚከናወኑ ዘመቻዎች የሚያገለግል በጣም ፈጣን የወታደር ማውረጃ እና ማጓጓዣ ጀልባ፣

19 ወታደሮችን የመጫን አቅም አለው፣

የተኩስ ድጋፍ፣ ለድንገተኛ ሕክምና ማንቀሳቀሻ እና የባሕር ላይ ወንበዴነት መከላከያ አቅም፣

ከፍተኛ ፍጥነት፦ በሰዓት 78 ኪሜ፣

የመጓዣ ርቀት አቅም፦ ቢያንስ 741 ኪ.ሜ፣

ብረት ለበስ ክፍሎች፣ የወታደሮች ማደሪያ ክፍል እና ሞተሮች፤

የትጥቅ አማራጮች፦ መትረየስ፣ የርቀት ውጊያ መሣሪያዎች መቆጣጠሪያ ወይም የቦምብ ማስወንጨፊያ።

የጀልባዎቹን ሥራ የሚያስጀምሩ ቡድኖች ከሠለጠኑ የአፍሪካ የባሕር ኃይል አባላት ጋር አብረው እየሠሩ መሆናቸውን ተወካዩ ጠቁመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0