የሩሲያ ቢኬ-16ኢ ጀልባዎች በአፍሪካ የፀረ-ሽብር ዘመቻዎች ላይ በከፍተኛ ብቃት እያገለግሉ እንደሆነ አምራቹ ገለጸ
16:19 15.06.2026 (የተሻሻለ: 16:24 15.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሩሲያ ቢኬ-16ኢ ጀልባዎች በአፍሪካ የፀረ-ሽብር ዘመቻዎች ላይ በከፍተኛ ብቃት እያገለግሉ እንደሆነ አምራቹ ገለጸ
ግዙፉ የሩሲያ የአነስተኛ ጦር መሣሪያ አምራች ካላሽኒኮቭ፤ በዚህ ዓመት ሁለት የቢኬ-16ኢ ፈጣን የጥቃት ጀልባዎችን ለአንድ የአፍሪካ ደንበኛ ማድረሱንና ተጨማሪ አምስት ጀልባዎችን እየገነባ መሆኑን ገልጿል። ጀልባዎቹ በፀረ-ሽብር ዘመቻዎች ላይ ባሳዩት አፈጻጸም አዎንታዊ ግብረመልስ እንደተሰጣቸው የኩባንያው ተወካይ ለሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።
የቢኬ-16ኢ ጀልባዎች ዋና ዋና ባህሪያት፦
በባሕር ዳርቻዎች ለሚከናወኑ ዘመቻዎች የሚያገለግል በጣም ፈጣን የወታደር ማውረጃ እና ማጓጓዣ ጀልባ፣
19 ወታደሮችን የመጫን አቅም አለው፣
የተኩስ ድጋፍ፣ ለድንገተኛ ሕክምና ማንቀሳቀሻ እና የባሕር ላይ ወንበዴነት መከላከያ አቅም፣
ከፍተኛ ፍጥነት፦ በሰዓት 78 ኪሜ፣
የመጓዣ ርቀት አቅም፦ ቢያንስ 741 ኪ.ሜ፣
ብረት ለበስ ክፍሎች፣ የወታደሮች ማደሪያ ክፍል እና ሞተሮች፤
የትጥቅ አማራጮች፦ መትረየስ፣ የርቀት ውጊያ መሣሪያዎች መቆጣጠሪያ ወይም የቦምብ ማስወንጨፊያ።
የጀልባዎቹን ሥራ የሚያስጀምሩ ቡድኖች ከሠለጠኑ የአፍሪካ የባሕር ኃይል አባላት ጋር አብረው እየሠሩ መሆናቸውን ተወካዩ ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X