ቢያንስ 20 የአፍሪካ እና የእስያ የወሊድ ባለሙያዎች በፖርቱጋል ለሚካሄደው ዓለም አቀፍ ኮንግረስ ቪዛ ተከለከሉ
18:16 14.06.2026 (የተሻሻለ: 18:24 14.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ቢያንስ 20 የአፍሪካ እና የእስያ የወሊድ ባለሙያዎች በፖርቱጋል ለሚካሄደው ዓለም አቀፍ ኮንግረስ ቪዛ ተከለከሉ
በዓለም አቀፉ የአዋላጅ ነርሶች ኮንፌዴሬሽን ኮንግረስ ላይ እንዳይሳተፉ ከተከለከሉት መካከል የኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ ኡጋንዳ፣ ሴራሊዮን፣ ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ፣ ባንግላዲሽ እና ሕንድ የወሊድ ባለሙያዎች እንደሚገኙበት መገናኛ ብዙኃን ገልጸዋል።
“በየሁለት ደቂቃው አንዲት እናት በወሊድ ምክንያት ትሞታለች። ይህ የቪዛ ክልከላ ድምፃቸው ይበልጥ ሊሰማ የሚገባቸውን ባለሙያዎች የሚያፍን ነው” ሲሉ የማህፀንና የወሊድ ባለሙያዎች ኮንፌዴሬሽን አማካሪ ኬት ስትሪንገር ተናግረዋል።
“ከበለጸጉ” ሀገራት የመጡ ልዑካን በሙሉ እንዲገቡ መፈቀዱን በመጥቀስ፤ ሁኔታውን ከእግር ኳስ ዳኛው ኡመር አርታን ክስተት ጋር በማነጻጸር “የቅኝ ግዛት አድልዎ” መገለጫ ነው ሲሉ ኮንነውታል።
ዓለም አቀፉ የወሊድ ባለሙያዎች ኮንግረስ፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ የሚከሰተውን የ260 ሺህ እናቶች ሞት እንዲሁም በተወለዱ በመጀመሪያው ወር ውስጥ የሚሞቱ 4.2 ሚሊዮን ጨቅላ ህጻናትን ቁጥር ለመቀነስ ያለመ የውይይት መድረክ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X