ታላላቆቹ የቡድን 20 ኢኮኖሚዎች አሜሪካ በሩሲያ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ እንድታቀል ከመጋረጃ ጀርባ እየጠየቁ እንደሆነ ተገለጸ

© telegram sputnik_ethiopiaታላላቆቹ የቡድን 20 ኢኮኖሚዎች አሜሪካ በሩሲያ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ እንድታቀል ከመጋረጃ ጀርባ እየጠየቁ እንደሆነ ተገለጸ
ታላላቆቹ የቡድን 20 ኢኮኖሚዎች አሜሪካ በሩሲያ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ እንድታቀል ከመጋረጃ ጀርባ እየጠየቁ እንደሆነ ተገለጸ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 14.06.2026
ሰብስክራይብ

ታላላቆቹ የቡድን 20 ኢኮኖሚዎች አሜሪካ በሩሲያ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ እንድታቀል ከመጋረጃ ጀርባ እየጠየቁ እንደሆነ ተገለጸ

"እኛ እስከምናውቀው ድረስ በርካታ ታላላቅ ኢኮኖሚ ያላቸው ሀገራት የማዕቀቡ በትር የሚያስከትለውን ጎጂ ውጤት ለአሜሪካውያን በሚስጢር እያስረዱ ይገኛሉ። ሕገ-ወጥ ገደቦች በዓለም አቀፉ ኢኮኖሚ ላይ የተጋረጡ አደጋዎች እና ተግዳሮቶችን ከማባባስ የዘለለ ፋይዳ እንደሌላቸው ዋሽንግተንን ለማሳመን እየሞከሩ ነው" ሲሉ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቡድን 20 እና የእስያ-ፓስፊክ ኢኮኖሚ ትብብር ጉዳዮች ልዩ አምባሳደር ማራት ቤርዲየቭ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

​ይሁን እንጂ በቡድን 20 ይፋዊ የውይይት መድረኮች አሜሪካ በሩሲያ ነዳጅ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ስለማቃለል በቀጥታ እንዳላነሱም አብራርተዋል።

የአሜሪካ የኢነርጂ ሚኒስትር ክሪስ ራይት፤ በቡድን 20 አባል ሀገራት ጥያቄ መሠረት፤ ዋሽንግተን ከሩሲያ በባሕር ለሚጓጓዙ የነዳጅ ጭነቶች የሰጠችውን የማዕቀብ እፎይታ እንዳራዘመች ባሳለፍነው ሚያዚያ ወር ገልጸው ነበር። የዩናይትድ ስቴትስ የገንዘብ ሚኒስትር ስኮት ቤሰንት፤ አሜሪካ ግንቦት 8 ቀን የተጠናቀቀውን ይህንኑ የማዕቀብ እፎይታ ለተጨማሪ 30 ቀናት እንዳራዘመች አስታውቀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0