የኢትዮጵያ እና ሩሲያ የባዮሎጂ ማዕከል ማቋቋሚያ ስምምነት፤ ኢትዮጵያን ተጠቃሚ ያደርጋታል - የፓርላማ አባል
08:31 14.06.2026 (የተሻሻለ: 08:34 14.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ እና ሩሲያ የባዮሎጂ ማዕከል ማቋቋሚያ ስምምነት፤ ኢትዮጵያን ተጠቃሚ ያደርጋታል - የፓርላማ አባል
ስምምነቱ በግብርናው ዘርፍ ያልተነኩ እምቅ አቅሞችን በማንቀሳቀስ ለሀገሪቱ ለውጥ ኃይል እንደሚሆኑ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።
ማዕከሉ የሁለቱን ሀገራት የጋራ የሳይንስ እና ምርምራ ትብብር እንደሚያሳድግ እና ተቋማዊ እንደሚያደርግ የሕዝብ እንደራሴው ጨምረው ተናግረዋል።
"የዚህ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል መቋቋም ሁለቱንም ሀገራት፤ በተለይም ኢትዮጵያን ተጠቃሚ ያደርጋል። በሁለቱ ሀገራት መካከል ቀድሞውኑ በፕሮጀክት ደረጃ እየተካሄዱ ያሉ የምርምር ሥራዎች አሉ። እናም እነዚህን ግንኙነቶች ተቋማዊ ለማድረግ እና በማጠናከር፤ የሰው ሀብት ልማትን፣ የአቅም ግንባታን እንዲሁም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የምርምር መሠረተ ልማትን ለማሳደግ ያስፈልገናል።"
የማዕከል ማቋቋሚያ ስምምነቱ "በዓሣ ሀብት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ፣ የሰብል ልማት፣ የአካባቢ ጥበቃ እና በጤናው ዘርፍ ጭምር የኢትዮጵያን ያልተነካ እምቅ አቅም ወደ እውነተኛ ሀብትነት ለመለወጥ ይረዳል" ሲሉም ፈትሂ ማህዲ አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X