የኢራን እና የአሜሪካ የሰላም ስምምነት በሚቀጥሉት 24 ሰዓታት ውስጥ ሊጠናቀቅ እንደሚችል የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ገለጹ
15:39 13.06.2026 (የተሻሻለ: 15:44 13.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢራን እና የአሜሪካ የሰላም ስምምነት በሚቀጥሉት 24 ሰዓታት ውስጥ ሊጠናቀቅ እንደሚችል የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ገለጹ
ፓኪስታን በሚቀጥሉት 24 ሰዓታት ውስጥ ለሚከናወነው የአሜሪካ እና የኢራን የሰላም ስምምነት የዲጂታል (የኤሌክትሮኒክስ) ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ዝግጅቷን አጠናቀለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሻሪፍ ተናግረዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሌሎች ንግግሮች፦
የስምምነቱ ፊርማ ከተከናወነ በኋላ በሚቀጥለው ሳምንት የቴክኒክ ደረጃ ውይይቶች ይካሄዳሉ ተብሎ ታቅዷል።
ፓኪስታን አሜሪካ እና ኢራን በኢስላማባድ ለተደረገው ውይይት ላሳዩት ቁርጠኝነት አድናቆቷን ትገልጻለች።
ሻሪፍ ለሂደቱ ድጋፍ ላደረጉ የክልሉ ሀገራትም ምሥጋና አቅርበዋል።
ስምምነቱ ለዘላቂ ሰላም መሠረት ሊጥል እንደሚችል ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X