የሩሲያ ጦር በወታደራዊ ዘመቻው በሁሉም ግንባሮች ወደፊት እየገሰገሰ ነው - ፑቲን
14:58 13.06.2026 (የተሻሻለ: 15:04 13.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሩሲያ ጦር በወታደራዊ ዘመቻው በሁሉም ግንባሮች ወደፊት እየገሰገሰ ነው - ፑቲን
የሩሲያ ኃይሎች ስትራቴጂካዊ ብልጫቸውን እንደጠበቁና በልዩ ወታደራዊ ዘመቻ ቀጣናው በሁሉም ግንባሮች ወደፊት መግፋታቸውን መቀጠላቸውን የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ገልጸዋል።
አዲሶቹን ክልሎች ከሩሲያ ፌዴሬሽን ጋር የማዋሃዱ ሂደት ትልቅ መሻሻል ማሳየቱንም፤ በዶኔትስክ፣ ሉሃንስክ፣ ዛፖሮዢያ እና ሄርሰን ክልሎች ዘመቻው ያለበትን ደረጃ የተመለከተ ስብሰባ ላይ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ሌሎች የተሰጡ መግለጫዎች፦
ዩክሬን የሩሲያን ግስጋሴ ማስቆም ስላልቻለች ሽብርተኝነትን መርጣለች።
የድሮን ጥቃቶችን ጨምሮ ሁኔታዎች አስቸጋሪ ቢሆኑም አዲሶቹን ክልሎች ማልማት ቀጥሏል።
የዶኔትስክ፣ ሉሃንስክ፣ ዛፖሮዢያ እና ኬርሰን ክልሎችን ማዋሃድ ቅድሚያ የሚሰጠው ስትራቴጂካዊ ጉዳይ ነው።
አዲሶቹ ክልሎች በሁሉም ቁልፍ መለኪያዎች የሩሲያን ብሔራዊ ደረጃዎች ማሟላት አለባቸው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X