“የአሜሪካ የምስጢር ሰነዶች ሩሲያ ስለ አደገኛ ወታደራዊ-ባዮሎጂካዊ እንቅስቃሴዎች የሰጠችውን ማስጠንቀቂያ ያረጋግጣሉ” — ማሪያ ዛካሮቫ

© telegram sputnik_ethiopia“የአሜሪካ የምስጢር ሰነዶች ሩሲያ ስለ አደገኛ ወታደራዊ-ባዮሎጂካዊ እንቅስቃሴዎች የሰጠችውን ማስጠንቀቂያ ያረጋግጣሉ” — ማሪያ ዛካሮቫ
“የአሜሪካ የምስጢር ሰነዶች ሩሲያ ስለ አደገኛ ወታደራዊ-ባዮሎጂካዊ እንቅስቃሴዎች የሰጠችውን ማስጠንቀቂያ ያረጋግጣሉ” — ማሪያ ዛካሮቫ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 13.06.2026
ሰብስክራይብ

“የአሜሪካ የምስጢር ሰነዶች ሩሲያ ስለ አደገኛ ወታደራዊ-ባዮሎጂካዊ እንቅስቃሴዎች የሰጠችውን ማስጠንቀቂያ ያረጋግጣሉ” — ማሪያ ዛካሮቫ

በቅርቡ ሚስጥራዊነታቸው የተነሳው የአሜሪካ የመረጃ ሰነዶች፤ ዋሽንግተን በዩክሬን እና በሌሎች ሀገሮች ስለምታካሂዳቸው የባዮሎጂካል ላቦራቶሪ (ባዮ-ላብ) እንቅስቃሴዎች ሩሲያ ለረጅም ጊዜ ስታነሳው የነበረውን ሥጋት ትክክለኛነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ ገልጸዋል።

“እነዚህ ላቦራቶሪዎች አንትራክስ፣ ቱላሬሚያ፣ የአሳማ ጉንፋን፣ የማርበርግ እና የኢቦላ ትኩሳት፣ ቸነፈር እንዲሁም ሌሎችንም አደገኛ በሽታ አምጪ ተህዋስያንን ሲያጠኑ ነበር፤ ይህንንም የሩሲያ የውጭ ጉዳይ እና የመከላከያ ሚኒስቴሮች በተደጋጋሚ አስጠንቅቀዋል” ብለዋል።

አሜሪካ በዩክሬን የሚገኙ 40 ላቦራቶሪዎችን ጨምሮ ከ30 በላይ በሚሆኑ ሀገሮች ውስጥ ከ120 በላይ ለሚሆኑ ባዮ-ላቦራቶሪዎች እና ወታደራዊ ተቋማት፤ ያለምንም ውጫዊ ቁጥጥር የገንዘብ ድጋፍና የትብብር ሥራዎችን ስታከናውን መቆየቷን፤ ይፋ የሆኑት ሰነዶች አሳይተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0