"አፍሪካ ሉዓላዊነቷን ሳትገብር ከዓለም ጋር መነገድ አለባት" - ባለሙያው አሜሪካ በአጎአ በኩል በአኅጉሪቱ ላይ ስለምትታደርገው ጫና ተናገሩ
"አፍሪካ ሉዓላዊነቷን ሳትገብር ከዓለም ጋር መነገድ አለባት" - ባለሙያው አሜሪካ በአጎአ በኩል በአኅጉሪቱ ላይ ስለምትታደርገው ጫና ተናገሩ
"አዲሱ ቅኝ ግዛት እየመጣ ያለው ከወታደራዊ ወረራ ይልቅ በውሎች፣ በንግድ ቅድመ-ሁኔታዎች እና በገበያ ተደራሽነት መስፈርቶች ነው" ሲሉ የኬንያው የመንግሥት አስተዳደር እና የኢኮኖሚክስ ባለሙያ ፍሬድሪክ ኦንያንጎ ኦጎላ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
እንደ ኦጎላ ገለጻ፣ አፍሪካ በሚከተሉት ነጥቦች ምክንያት ወሳኝ የመደራደር ብልጫ አላት፦
🟠 እያደገ ያለ የሕዝብ ቁጥር፣
🟠 እየሰፉ ያሉ ገበያዎች፣
🟠 ሰፊ የግብርና እምቅ አቅም እና
🟠 ወሳኝ የሆኑ ማዕድናት።
"አፍሪካ ከአፍሪካ የእድገትና ዕድል አዋጅ (አጎአ)፣ ከዕርዳታ እና ከልዩ ጥቅም የሚሻገሩ ኢንዱስትሪዎችን መገንባት አለባት" ሲሉም አክለዋል።
"የንግድ ጫና ምርጡ መከላከያ መጋፈጥ አይደለም። ይልቁንም ራስን መቻል፣ ቀጣናዊ አንድነት እና ጠንካራ ተቋማት ናቸው።"
ℹ ቀደም ሲል የአሜሪካ የሥጋ ኢንዱስትሪ እንደ ኬንያ፣ ናይጄሪያ እና ደቡብ አፍሪካ ያሉ የአፍሪካ ሀገራት ገበያቸውን ለአሜሪካ የበሬ እና የአሳማ ሥጋ ወጪ ንግድ እንዲከፍቱ ለማስገደድ፣ የአሜሪካ የንግድ ተወካይ ቢሮ የአጎአ ማሻሻያን እንደ ማስገደጃ መሣሪያ እንዲጠቀምበት በይፋ ጠይቆ ነበር።
አሜሪካ የአጎአን ትኩረት ከአስተዳደር ጉዳዮች ወደ ገበያ ተደራሽነት ጉዳዮች ለምን እንዳዛወረች እና የ"አፍሪካ ጠንካራ ምላሽ" ምን እንደሚሆን ለማወቅ ቪዲዮውን ይመልከቱ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X