- Sputnik አፍሪካ, 1920
Drum of Changes
ከጥንታዊ የስልጣኔ ምድሮች እስከ ዘመናዊ ከተሞች ልብ፣ በአፍሪካ አዲስ ጥሪ እየተስተጋባ ይገኛል። አፍሪካ የዓለምን የወደፊት ሁኔታ የምትቀርጽ ቸል ልትባል የማይገባት ኃይል ሆና እያደገች ነው። ለአስርት ዓመታት አፍሪካ የምትናገር፣ ነገር ግን የማትደመጥ ሆና ቆይታለች። ዛሬ ግን ጥሪው ግልፅ ነው። አፍሪካ ከዓለም የኃይል ማዕድ የሚገባትን ትክክለኛ ቦታ ትጠይቃለች። ይህ ፕሮግራምም ከአፍሪካ የሚስተጋቡ የለውጥ ድምፆችን በልካቸው ወደ አድማጭ ተመልካቾቹ ያደርሳል።

ከቅድመ-ሁኔታዎች ጋር ከተያያዘ ዕርዳታ ባሻገር፡ ለአፍሪካ የጤና ዋስትና ሉዓላዊ የፋይናንስ አቅምን መገንባት

ከቅድመ-ሁኔታዎች ጋር ከተያያዘ ዕርዳታ ባሻገር፡ ለአፍሪካ የጤና ዋስትና ሉዓላዊ የፋይናንስ አቅምን መገንባት
ሰብስክራይብ

የዚምባብዌ ሪፐብሊክ የኤቦላ ወረርሽኝን ለመከላከል ለአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል (አፍሪካ ሲዲሲ) የአንድ ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገንዘብ ድጋፍ አድርጋለች።
“በተበታተነ ሁኔታ ከምንንቀሳቀስ፣ ራሳችንን ለመጠበቅ [ከተለያዩ የጤና ቀውሶች] ካሉን ሀብቶች በመቀነስና በአንድ ላይ በማሰባሰብ፣ ትብብራችንን ማጠናከር፣ ዛሬ ህዝባችንን እየጎዱ ያሉትን የጤና ችግሮች ለመፍታት የሚያስፈልገውን የፋይናንስ አቅም መገንባት አለብን። የዚህ ጥረት አካል በመሆን [አፍሪካውያን ሁሉ] የሚያስፈልገንን ቀጥተኛ የፋይናንስ እቅም መፍጠር እንችላለን” ሲሉ የዚንባብዌ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የፖለቲካ ተንታኙ ላዛረስ ሳዉቲ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን፣ አፍሪካ የህዝብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎችን በራስ አቅም ስለመምራቷ የተመለከተ ጉዳይ እንወያያለን። ለዚህም በዚንባብዌ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህርና ተንታኝ ላዛረስ ሳዉቲን አነጋግረናል። በሁለተኛ ጉዳያቸን እ.ኤ.አ. ከሰኔ 11 እስከ 12 ቀን 2026 በአዲስ አበባ የተካሄደውን የመጀመሪያው የአፍሪካ ልማት ተፅዕኖ መድረክ ላይ እናተኩራለን።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripods Pocket CastsPodcast AddictCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0