"የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ብርሃነኢየሱስ ሐዋርያዊ ኃላፊነታቸውን አሰረከቡ" - የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ
16:34 12.06.2026 (የተሻሻለ: 16:44 12.06.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
"የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ብርሃነኢየሱስ ሐዋርያዊ ኃላፊነታቸውን አሰረከቡ" - የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ
ሊቀጳጳስ በጡረታ ምክንያት ለቅድስት መንበር ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ በዛሬው ዕለት ጥያቄያቸውን መቀበላቸውን በቅድስት መንበር ልዩ መልዕክተኛ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ አማካይነት ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ይፋ መደረጉን ጉባኤው በማኅበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ አስታውቋል።
የብፁዕ አቡነ ብርሃነኢየሱስ በፈቃዳቸው ከኃላፊነት መልቀቃቸውን የቤተክርስቲያኗ ምንጮች ለስፑትኒክ አፍሪካ አረጋግጠዋል፡፡
የብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ ተተኪ በመሆን የአዲስ አበባ ረዳት ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ተስፋሥላሴ የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ ሆነው መሾማቸውም ተመላክቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X