የሩሲያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከኮንጎ ሪፐብሊክ ጋር የተደረሰውን የኢንቨስትመንት ጥበቃ ስምምነት አጸደቀ

© telegram sputnik_ethiopiaየሩሲያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከኮንጎ ሪፐብሊክ ጋር የተደረሰውን የኢንቨስትመንት ጥበቃ ስምምነት አጸደቀ
የሩሲያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከኮንጎ ሪፐብሊክ ጋር የተደረሰውን የኢንቨስትመንት ጥበቃ ስምምነት አጸደቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 10.06.2026
ሰብስክራይብ

የሩሲያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከኮንጎ ሪፐብሊክ ጋር የተደረሰውን የኢንቨስትመንት ጥበቃ ስምምነት አጸደቀ

እ.ኤ.አ. በጥቅምት 2025 የተፈረመው ይህ ስምምነት፤ የሁለቱም አገራት ባለሀብቶች የረጅም ጊዜ ሕጋዊ ዋስትና እና መረጋጋት እንዲኖራቸው ለማድረግ ያለመ መሆኑን ባለሥልጣናት ገልጸዋል።

ዋና ዋና ዝርዝሮች፦

በሩሲያ እና በኮንጎ ሪፐብሊክ መካከል ያለውን የንግድ እና የኢኮኖሚ ትብብር ያጠናክራል ተብሎ ይጠበቃል።

ማናቸውም አለመግባባቶች በዱባይ ዓለም አቀፍ የግልግል ዳኝነት ማዕከል የሚታዩ ሲሆን፤ ስምምነቱ ለባለሀብቶች “ይበልጥ ተመራጭ አገር” የሚሰጠውን ዓይነት መብትና እንክብካቤን ያካትታል።

በጋራ መግባቢያው መሠረት፤ የዓለም የንግድ ድርጅት የደህንነት እና አጠቃላይ ልዩ ሁኔታዎች እንዲሁም የጥንቃቄ እርምጃዎች ተፈጻሚነት ይኖራቸዋል።

በማጽደቂያ ሕጉ መሠረት፤ የሩሲያ ፍርድ ቤቶች ወይም ዓለም አቀፍ የግልግል ዳኝነት በሚወስኑት መሠረት፣ የኮንጎ ባለሀብቶች ንብረታቸው ከተወረሰ ወይም ጉዳት ከደረሰባቸው ሩሲያ ካሳ ትከፍላለች። ኮንጎም በተመሳሳይ መልኩ ተመሳሳይ ግዴታዎችን ትወስዳለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0