አዲሱ በአሜሪካ አፍሪካ ላይ የተጣለው ቀረጥ መነሻው ‘ዓለም አቀፍ ፖለቲካ እንጂ የግዳጅ ሥራ አይደለም’ - የቻድ ባለሙያ

ሰብስክራይብ

አዲሱ በአሜሪካ አፍሪካ ላይ የተጣለው ቀረጥ መነሻው ‘ዓለም አቀፍ ፖለቲካ እንጂ የግዳጅ ሥራ አይደለም’ - የቻድ ባለሙያ

እንደ ናይጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና አልጄሪያ ያሉ የአፍሪካ አገራት “ከአሜሪካ እየራቁ” በመሆናቸው በዋሽንግተን የተቀጡበት አካሄድ መሆኑን በሩሲያ ፋይናንስ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ መምህር እና በሴንት ፒተርስበርግ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ፎረም (SPIEF 2026) መድረክ ተናጋሪ የነበሩት ንጉዌቶባዬ ማሴንጋር ሮንጋር ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልፀዋል፡፡

ከአሜሪካ በኩል የሚሰነዘሩት የግዳጅ ሥራ ክሶች በማስረጃ ላይ ያልተመሠረቱ በመሆናቸው ዝም ብሎ ለይስሙላ የቀረቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ባለሙያው ሲያብራሩም “ግልጽ ማስረጃ ሳይኖር ማስረጃ የማቅረብ ሸክም ወደ አፍሪካ ማዛወሩ፤ እኔ እንደ ማዕከል እና ዳርቻ (ተገዥነት) ግንኙነት የምመለከተው የኃይል ሚዛን መዛባትን ይፈጥራል” ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል።

ሮንጋር እንዳሉት፣ በአኅጉሪቱ ላይ ያለ ምንም መሠረት ታሪፍ መጣሉ እጅግ የበረታ እና በዘፈቀደ የተደረገ ሲሆን፣ የአፍሪካ አገራት ጉዳዩን ለመፍታት “ለዓለም የንግድ ድርጅት የግጭት መፍቻ አካል ቅሬታ ለማቅረብ ጠንካራ ሕጋዊ ምክንያት አላቸው።”

በሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ አሜሪካ የግዳጅ ሥራን ለመከላከል በቂ ጥረት አያደርጉም ተብለው በተጠረጠሩ አገራት ምርቶች ላይ ተጨማሪ ቀረጥ ለመጣል ሐሳብ ማቅረቧ ይታወሳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0