ፍርድ ቤት በሙግት መድረክ፦ ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት የታማኝነት ፈተናውን ያልፍ ይሆን? - የጆርዳኑ ባለሙያ ምልከታቸውን አጋርተዋል
13:34 10.06.2026 (የተሻሻለ: 13:44 10.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ፍርድ ቤት በሙግት መድረክ፦ ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት የታማኝነት ፈተናውን ያልፍ ይሆን? - የጆርዳኑ ባለሙያ ምልከታቸውን አጋርተዋል
ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት የሚንቀሳቀሰው ከፖለቲካ ተጽዕኖ ነፃ በሆነ ገለልተኛ ምሕዳር ውስጥ ሳይሆን፣ በፖለቲካ ሴራዎች መናኸሪያ እና በከፍተኛ ጫና ውስጥ ነው ሲሉ በጆርዳን ዩኒቨርሲቲ የሕገ-መንግሥት ሕግ ፕሮፌሰር ላይዝ ካማል ናስራዊን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
ባለሙያው ይህንን ያሉት የፍርድ ቤቱ ዓቃቤ ሕግ ካሪም ኻን በትንኮሳ ክስ ከሥራ መታገዳቸውን ተከትሎ በሰጡት አስተያየት ነው።
“በአንድ በኩል ፍርድ ቤቱ ሁሉንም ሰው በፍትሐዊነት እና በእኩልነት የመዳኘት ግዴታ አለበት። በሌላ በኩል ደግሞ አገራት በሥልጣን እና በተጽዕኖ ደረጃ በፈጥሯቸው እኩል ባልሆኑበት ዓለም ውስጥ የመኖር እና የመቀጠል ግዴታ አለበት” ሲሉ ጠቁመዋል።
በካሪም ኻን ዙሪያ የተነሳው ይህ ቅሌት ለፍርድ ቤቱ የእውነት መገለጫ ቅጽበት ነው፤ ሆኖም ግን ራሱን ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት “ለዘለቄታው አይቀብረውም” ሲሉ ባለሙያው አፅንዖት ሰጥተዋል።
ያም ሆኖ ግን በፈረንሳይና በሌሎች አገራት ጭምር የሚጠቀሰው ይህ በፍርድ ቤቱ ዓቃቤ ሕግ ላይ የቀረበው ክስ፣ በራሱ በዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ስም ላይ ጥላሸት የሚቀባ አደገኛ ቅድመ-ሁኔታን የሚፈጥር ነው ሲሉ ናስራዊን ገልጸዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ቪዲዮ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X