በምዕራባውያን የሚጫነውን ዲሞክራሲ ውድቅ ማድረግ - ኬንያዊ ባለሥልጣን የሳሚያ ሱሉሁ ሐሰን እና ፑቲንን የርዕይ መጣጣም አደነቁ
08:34 10.06.2026 (የተሻሻለ: 08:44 10.06.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በምዕራባውያን የሚጫነውን ዲሞክራሲ ውድቅ ማድረግ - ኬንያዊ ባለሥልጣን የሳሚያ ሱሉሁ ሐሰን እና ፑቲንን የርዕይ መጣጣም አደነቁ
የኬንያው ሕግ ባለሙያ እና የፓርላማ ጸሐፊ አህመድ አብዱልአዚዝ ካዲ እንደገለጹት፤ በሩሲያው ፕሬዝዳንት እና በታንዛኒያ አቻቸው መካከል የተደረገው ታሪካዊ ስብሰባ በስትራቴጂካዊ ርዕያቸው ላይ ያላቸውን ጥልቅ መጣጣም ያሳያል።
ሁለቱ መሪዎች በማታለል ላይ በተመሠረቱ የገንዘብ ምንዛሬዎች፣ የባንክ ሥርዓቶች ወይም በብዝበዛ ስምምነቶች አማካኝነት የሚደረገውን የአዲስ ቀኝ ግዛት ቁጥጥር የማፍረስ እና ለአገሮቻቸው እውነተኛ ሉዓላዊነትን የመመለስ የጋራ ቁርጠኝነት አላቸው ሲሉ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ካዲ አፅንዖት ሰጥተው እንደገለጹት፣ ከጂኦፖለቲካዊ ግቦቻቸው ባሻገር ሁለቱም ፕሬዚዳንቶች በሚያስደንቅ ሁኔታ ተመሳሳይ የጥበብ አመራር ዘይቤ ያሳያሉ፤ ምክንያቱም ሁለቱም መሪዎች፦
🟠 እርስ በርስ ግልጽ እና ቀጥተኛ ውይይት ያደርጋሉ፡፡
🟠 ለተለያዩ ባህሎች ጥልቅ ክብር ያሳያሉ፡፡
🟠 በትህትና የተሞላ ቋንቋ እና የተራቀቀ ሥነ-ምግባር በመጠቀም ይግባባሉ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X