የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ታሪካዊ የሩሲያ ጉብኝት የ60 ዓመታት ግንኙነትን ያደሰ፤ ለሩሲያ ኢንቨስትመንትም መንገድ የጠረገ ነው - የደቡብ አፍሪካ ባለሙያ
የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ታሪካዊ የሩሲያ ጉብኝት የ60 ዓመታት ግንኙነትን ያደሰ፤ ለሩሲያ ኢንቨስትመንትም መንገድ የጠረገ ነው - የደቡብ አፍሪካ ባለሙያ
የልማት ፋይናንስ ባለሙያ ዶ/ር ታፋድዝዋ ሩዚቭ ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት፤ ሳሚያ ሱሉሁ ሐሰን በቅርቡ በሩሲያ ያደረጉት ይፋዊ የመንግሥት ጉብኝት እ.ኤ.አ. ከ1969 ወዲህ በአንድ የታንዛኒያ መሪ የተደረገው የመጀመሪያው ሲሆን ዶዶማ ስልታዊ አቅጣጫዋን ወደ ምሥራቅ ማዞሯን ያሳያል።
ይህ ጉብኝት በሚቀጥሉት ከሦስት እስከ አምስት ዓመታት ውስጥ በቱሪዝም፣ በአቪዬሽን፣ በኒውክሌር ምርምር፣ በጤና፣ በሎጅስቲክስ እና በክትባት ምርት ላይ ያተኮረ ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሩሲያ ኢንቨስትመንትን ይስባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል።
ዶ/ር ሩዚቭ “የኢንቨስትመንት መጎረፉ ታንዛኒያን በምሥራቅ አፍሪካ ካላት ድምፅ አልባ ተፅዕኖ በማውጣት፣ ለባሕር ላይ እና ለሎጅስቲክስ ኢንቨስትመንቶች የቀጣናው መልሕቅ ወደ መሆን ግንባር ቀደም ተዋናይነት እንድትመለስ ያግዛታል” ብለዋል።
በሩሲያ ድጋፍ የሚገነባው የክትባት ማምረቻ ተቋም የታንዛኒያን የጤና ሉዓላዊነት የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ ለምሥራቅና ደቡብ አፍሪካ ማዕከል ሆኖ ያገለግላል፤ ይህም በምዕራባውያን ቅድመ ሁኔታዎች ላይ የተመሠረተውን የጤና ዕርዳታ ጥገኝነት ይቀንሳል ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል።
ጉብኝቱ በደቡብ-ደቡብ መካከል የሚደረገውን ኢንቨስትመንት በማጠናከር እና ለአፍሪካ በምሥራቅ አፍሪካ የባሕር ጠረፍ ላይ ጠንካራ ጂኦፖለቲካዊ መሠረት በመስጠት የዓለም አቀፉን ደቡብ ንፍቀ ክበብ አቋም ያጠናክራል ሲሉ ባለሙያው ማጠቃለያቸውን ሰጥተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X