የኮንጎ ባለሥልጣናት የኢቦላ ስርጭት ሊባባስ እንደሚችል አስጠነቀቁ

የኮንጎ ባለሥልጣናት የኢቦላ ስርጭት ሊባባስ እንደሚችል አስጠነቀቁ
በቡንዲቡግዮ የኢቦላ ወረርሽኝ ዝርያ ዙሪያ የተሰሙ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች፦
ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
▪ የኮንጎ ጤና ሚኒስቴር ግንቦት 29 ቀን ባወጣው ሪፖርት፤ “ተገቢ የሆኑ እርምጃዎች በአስቸኳይ ካልተወሰዱ የሕመምተኞች ቁጥር ሊጨምር ይችላል” ሲል አስጠንቅቋል።
▪ የሀገሪቱ የጤና ባለሥልጣናት ከግንቦት 6 እስከ 15 ባለው ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች በበሽታው መያዛቸው መረጋገጡ፤ “ከአንድ የጋራ ምንጭ ከፍተኛ የመጋለጥ እና የሥርጭት ሁኔታ መኖሩን” ይጠቁማል ብለዋል።
▪ በወረርሽኙ እንደተያዙ የተረጋገጡ ሰዎች ቁጥር 515 የደረሰ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 91 የሚሆኑት ሕይወታቸው ማለፉን ባለሥልጣናቱ ጨምረው ገልጸዋል።
▪ ሦስት ተጨማሪ ታካሚዎች ከበሽታው ማገገማቸውን ተከትሎ አጠቃላይ ከበሽታው የዳኑ ሰዎች ቁጥር 12 ደርሷል።
ኡጋንዳ
▪ በሳምንቱ መጨረሻ ሦስት አዳዲስ የኢቦላ ጉዳዮች መመዝገባቸውን ተከትሎ አጠቃላይ በቫይረሱ እንደተያዙ የተረጋገጡ ሰዎች ቁጥር 19 መድረሱን የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር ቅዳሜ አስታውቋል።
▪ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ አድኃኖም የኡጋንዳን ጠንካራ አመራር እና የድንበር ተሻጋሪ ትብብር አወድሰዋል።
የበሽታ መከላከል ምላሽ
▪ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በሀገሪቱ የመከላከያ እርምጃዎችን ለማጠናከር 19.5 ሚሊዮን ዶላር እንደምታንቀሳቅስ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።
▪ ዚምቧቤ ለአፍሪካ ኅብረት የጤና ኤጀንሲ አፍሪካ ሲዲሲ 1 ሚሊዮን ዶላር እንደምትለግስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሞን ሙርዊራ ይፋ አድርገዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X