የናይጄሪያ ጦር በቦርኖ ግዛት ባካሄደው ዘመቻ 360 ታጋቾችን ነፃ አወጣ

ሰብስክራይብ

የናይጄሪያ ጦር በቦርኖ ግዛት ባካሄደው ዘመቻ 360 ታጋቾችን ነፃ አወጣ

ሴቶችና ሕፃናትን ጨምሮ ታጋቾቹ ነፃ የወጡት በደቡባዊ ቦርኖ ግዛት በማንዳራ ተራሮች ውስጥ በጠንካራ ምሽግ ከተጠበቁ የአሸባሪዎች መሸሸጊያ እንደሆነ የሀገሪቱ ጦር በማኅበራዊ ሚዲያ አስታውቋል።

"ሀዲን ካይ" የሚል የኮድ ስም የተሰጠው የፀረ-ሽብርተኝነት ዘመቻ የቦኮ ሀራም* እና የኢስዋፕ ቡድን አክራሪዎችን ኢላማ ያደረገ ነበር።

ታጋቾቹ በኃይል ታፍነውና በቁጥጥር ስር ውለው የቆዩ መሆናቸውን የጠቀሰው ወታደራዊ ኃይሉ፣ የነፃ ማውጣት ተልዕኮው በጥናትና በደህንነት መረጃዎች ላይ የተመሠረተ እንዲሁም እጅግ የተሳካ እንደነበር ገልጿል።

*ናይጄሪያ እና ሩሲያን ጨምሮ በሌሎች ሀገራት የታገዱ አሸባሪ ድርጅቶች

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopiaየናይጄሪያ ጦር በቦርኖ ግዛት ባካሄደው ዘመቻ 360 ታጋቾችን ነፃ አወጣ
የናይጄሪያ ጦር በቦርኖ ግዛት ባካሄደው ዘመቻ 360 ታጋቾችን ነፃ አወጣ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 07.06.2026
አዳዲስ ዜናዎች
0